the impact of ict on public service in amhara region governmental organizations

95
የዳሰሳ ጥናት የጥናት ቡድኑ አባላት 1) ጌታቸው መለሰ(/) 2) አቶ ጌታነህ አያሌው 3) አቶ ዑመር አደም 4) /ብርቱካን ገላው በአብክመ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ልማት ኤጄንሲ ባህር ዳር - ኢትዮጵያ ግንቦት 2004 ዓ.ም

Upload: getachew-melesephd

Post on 30-Oct-2014

135 views

Category:

Documents


4 download

TRANSCRIPT

Page 1: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

የዳሰሳ ጥናት

የጥናት ቡድኑ አባላት 1) ጌታቸው መለሰ(ዶ/ር) 2) አቶ ጌታነህ አያሌው 3) አቶ ዑመር አደም 4) ወ/ሮ ብርቱካን ገላው

በአብክመ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ልማት ኤጄንሲ ባህር ዳር - ኢትዮጵያ

ግንቦት 2004 ዓ.ም

Page 2: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

የፕላዝማ ውስጣዊ እይታ

Wireless Access Point

Page 3: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

i

ምስጋና

የጥናት ቡድኑ ጥናቱን በሚያካሂድበት ጊዜ መጠይቆችን ለተጠኝዎች እንዲደርሱና

ተሞልተው ለቡድኑ እዲመለሱ በማድረግ ሙያዊ አጋርነታቸውን በማበርከት ቀና ትብብር

ላደረጉልን የአብክመ ክልል ቢሮዎች፣ የዞንና የወረዳ ኢኮቴ ባለሙያዎች፤ መጠይቁን

በመሙላትና ለምልከታችን መረጃ በመስጠት የተባበሩንን ተጠኝዎች እንዲሁም

የተሰበሰበውን መረጃ ወደ ኮምፒውተር በማስገባት የተሳተፉትን ወ/ሮ አልማዝ

መሳፍንትንና ወ/ሪት አበባ ተኮላን የጥናት ቡድኑ ከልብ ያመሰግናል፡፡

Page 4: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

ii

አጽርኦተ ጥናት የዚህ ዳሰሳ ጥናት ዋና ዓላማ በአማራ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ያሳደረውን ተጽዕኖ መዳሰስ ነው፡፡ የዳሰሳ ጥናቱን

ለማካሄድ የሚያግዙ መረጃዎችን ለመሰብሰብ የጥናት ቡድኑ እኩል እድል የማይሰጥ

የናሙና አወሳሰድ ዘዴን ተጠቅሟል፤ በጥናቱ ውስጥ የተካተቱ ተጠኝዎች በዒላማ የናሙና

አወሳሰድ ዘዴ (Purposeful Sampling Method) ተመርጠዋል፡፡ የዳሰሳ ጥናቱ ሁለት

የመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎችን የተጠቀመ ሲሆን እነርሱም መጠይቅና ምልከታ ናቸው፡፡

የተሰበሰቡ መረጃዎች SPSS እና Microsoft Excel ሶፍትዌሮችን በመጠቀም

ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱን ውጤት ለማሳየትም ጥምርታ (Ratio) ፣ መቶኛ (Percent) ፣

አማካይ (Mean) ፣ ስታንዳርድ ዲቬሽን (Standard Deviation) እንዲሁም ኮርሌሽን

(Correlation) የተባሉት ስታትስቲካዊ መለኪያዎች ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡

የጥናቱ ውጤት እንደሚያመለክተው የወረዳኔት እና የስኩል ኔት ሽፋን ከፍተኛ መሆኑን

ስንረዳ ኢንተርኔት፣ የLAN ዝርጋታ፣ የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች ሽፋን መካከለኛ

ሲሆን የድረ-ገጽ ሽፋን ደግሞ ዝቅተኛ ነዉ፡፡ ለኢኮቴ የተሰጠ ትኩረት በአማካይ ዝቅተኛ

ነው፡፡ ለኢኮቴ የተሰጠዉ ትኩረት በጣም ዝቅተኛ ሆኖ የሚታየዉ ኢኮቴን አስመልክቶ

የተደረገ ጥናትና ምርምር አለመኖርና ራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል አለመኖር ናቸው፡፡

በአብዛኛዉ ሠራተኛ፣ ባለሙያ እና የበላይ ኃላፊ የኢኮቴ አገልግሎት በመንግስት

ተቋማት፣ እንደ ኢንተርኔት ካፌ ያሉ መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት አገልግሎቱን ሲያገኙ

ዝቅተኛ ቁጥር ያለዉ የመንግስት ሠራተኛ እቤቱ ድረስ አገልግሎቱን ያገኛል፡፡

ለኢኮቴ ተፅዕኖ አጠቃቀሙን ማሳደግ፤ አጠቃቀሙን ለማሳደግ ደግሞ ባለሙያዎች ብሎም

ሁሉም ሠራተኞች ክህሎቱ እንዲኖራቸዉ ማድረግ፤ የዕዉቀት አጠቃቀምና ተፅዕኖ

አዎንታዊ ኮርሌሽን እንዳላቸዉ እንደዚሁ ለተፅዕኖ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ

ሳይሆን ስልጠናና አቅርቦት አዎንታዊ ኮርሌሽን እንዳላቸዉ በዚህ ጥናት ተረጋግጧል፡፡

በአጫጭር የኢኮቴ ስልጠና በሚገኝ እውቀት ብቻ ብዙ አመት የስራ ልምድና የትምህርት

ደረጃ ሳይጠይቅ የአገልግሎት አሰጣጡን ማሻሻል እንደሚቻል ታይቷል፡፡ ከዚህ ጋር

ተያይዞ ለኢኮቴ ባለሙያዉ በተናጠል የአድቫንስድ ኮምፒዩተር ቋንቋ ስልጠና፣ ለኢኮቴ

መምህራን የትም/መረጃ ሲሙሌሽን ትዉዉቅና አጠቃቀም ስልጠና መስጠት ያሻል፡፡

Page 5: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

iii

በተለይ አይፒ ሚሴንጀር ኔትሚቲንግ ወዘተ. የመሳሰሉ ላን ቱልስ የአጠቃቀም ማንዋል

ማዘጋጀት ሁሉንም የተቋሙን ማህበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጥ ማስተዋወቅና ማሰልጠን

እንዲሁም ተግባራዊ መደረጉን መከታተል ያስፈልጋል፡፡

አብዛኛዉ የተቋማቱ ሠራተኞች የኮምፒዩተርና ተዛማጅ የኢኮቴ ዕቃዎች /መሳሪያዎች

ተጠቃሚ ሲሆኑ ኢንተርኔት፣ ወረዳኔት ወይም ስኩል ኔት፣ የLAN መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣

የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ተጠቃሚ ሰራተኞች ግን ጥቂት

ናቸዉ፡፡ የተቋማቸውን ድረ-ገጽ የሚጠቀሙ ደግሞ በጣም ጥቂቶች ናቸዉ፡፡ የኢኮቴ

መምህራን አልፎ አልፎ ቤተሙከራን የሚተካ ሲሙሌሽን በመጠቀም የሚየስተምሩ ሲሆን

በአጠቃላይ የኢኮቴ ባለሙያዉ ሁልግዜ የማይክሮ ሶፍት ወርድን በመጠቀም ደብዳቤ

ዶክመንት ወዘተ. ያዘጋጃሉ:: ሰራተኛውና የበላይ ሃላፊው ደግሞ በተደጋጋሚ

የማይክሮሶፍት ወርድን ይጠቀማሉ፡፡ የኢኮቴ ባለሞያው በተደጋጋሚ አብዛኛዉ ኃላፊና

ሠራተኛ ደግሞ አልፎ አልፎ ማክሮሶፍት ኤክሴል በመጠቀም ቻርት ፔሮል

ወዘተ.ያዘጋጃሉ፣ ፓወር ፖይንት በመጠቀም ስላይድ ያዘጋጃሉ፣ ኢሜል ይላላካሉ፡ እንደ

ጎግል ያሉ የመረጃ መበርበሪያ (Search Engine) እና በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-

መፃህፍት በመጠቀም መረጃ ያገኛሉ፣ የLAN መሰረተ ልማት ዝርጋታ በመጠቀም ሃብት

ይጋራሉ፣ የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞችን በመጠቀም መረጃ ይይዛሉ ያደራጃሉ:: የኢኮቴ

ባለሙያዉ አልፎ አልፎ የአይ.ፒ ሚሴንጀርና ኔትሚቲንግ የመሳሰሉ ላን ቱልስ

በመጠቀም የመረጃ ልውውጥና የመስመር ላይ ድጋፍ ያደርጋሉ ወይም ይቀበላሉ፤

አብዛኛዉ ኃላፊና ሠራተኛ ግን አይ.ፒ ሜሴንጀርና ኔትሚቲንግ አይጠቀምም ማለት

ይቻላል፡፡

በጥናቱ ከሰራተኛዉ፣ ከበላይ ኃላፊና ከኢኮቴ ባለሙያ በተሰበሰበ መረጃ መሰረት ኢኮቴ

ለአገልግሎት አሰጣጥ ፍጥነትና ጥራት መሻሻል፣ ዉጣ ዉረድን በመቀነስ፣ ደብዳቤ፣

ዶክመንት፣ ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ. በቀላሉ ለማዘጋጀት አስችሏል፡፡ ይህም አስተማማኝ

መረጃን በቀላሉ በማግኘትና በመለዋወጥ ሀብት፣ ጉልበት፣ ጊዜና ወጪን በመቆጠብ

ወረቀት አልባ የመረጃ ልዉዉጥ በማከናወን፣ የሰራተኛዉን ተነሳሽነት በመጨመር

እንዲሁም የሰራተኛዉንና የተቋሙን ሥራ አፈፃፀም በማሻሻል አዎንታዊ ተፅዕኖ

አሳድሯል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ ወረዳኔትና ስኩልኔት የቀጥታ የመስመር ላይ ድጋፍ

ለማድረግ ወይም ለመቀበል፣ በርቀት ዴስክቶፕ መረጃ ለመለዋወጥ፣ የተለያዩ የኢኮቴ

Page 6: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

iv

ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን በየአካባቢዉ በማድረስ ገንዘብ፣ ጊዜና ጉልበት በመቀነስ ረገድ

ምንም አይነት ተፅዕኖ አላሳደሩም፡፡

ከደንበኞች በተሰበሰበዉ መረጃ መሰረት የመንግስት አገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ፤

ዉጤታማ፤ ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ መቆጠቡ፤ ግልጽና ፍትሀዊ መሆኑ፤ በአጠቃላይ የመረጃ

አያያዝና አደረጃጀቱ በመሻሻሉ አወንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡

የመስሪያ ቤቱን ሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት በተመለከተም እንደዚሁ ከሁሉም ተጠኝዎች

ጋር በአማካይ ሲሰላ አዎንታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ተረጋግጧል፡፡ በይበልጥ በደንበኛዉ

እርካታ ረገድ ኢኮቴ አዎንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡ በአጠቃላይ ኢኮቴ በመንግስት

አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በአማካይ አዎንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡

በጥናቱ ውስጥ ቀልጣፋነት፣ ውጤታማነት፣ የደንበኞች እርካታ፣ ግልጽነት እና ፍትሃዊነት

በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ኢኮቴ ላሳደረው ተጽዕኖ አመልካቾች (Indicators)

ናቸው፡፡ ለአገልግሎት አሰጣጡ በጉልህ አወንታዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የማይክሮሶፍት

ወርድ፣ ኤክስኤል፣ ኢንተርኔትና የላን ዝርጋታ ናቸው፡፡

Page 7: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

አጽርዖተ ቃላት

o መመቴ - የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ

o አብክመ - የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት

o አይ.ፒ - ኢንተርኔት ፕሮቶኮል

o ኢኮቴ - ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ

o BPR – Business Processing Re-engineering

o CD – Compact Disk

o CDMA – Code Division Multiple Access

o ICT – Information Communication Technology

o LAN - Local Area Network

o MS – Microsoft

o RAM- Rand0m Access Memory

o SD - Standard deviation

o SIGTAS – Standard Integrate Government Tax Administration System

o WLAN – Wireless Local Area Network

Page 8: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

ማውጫ

ምዕራፍ አንድ ............................................................................................................... 1

1. መግቢያ ................................................................................................................... 1

1.1 የጥናቱ ዳራ .................................................................................................................................... 2 1.2 የጥናቱ መነሻ ሃሳብ ......................................................................................................................... 5 1.3 የጥናቱ ዓላማ .................................................................................................................................. 6 1.4 የጥናቱ ወሰን .................................................................................................................................. 7

1.5 የጥናቱ ውስንነት …………………………………………………………………………...7 ምዕራፍ ሁለት .............................................................................................................. 8 2. የተዛማጅ ፅሁፎች ክለሳ……………………………………………………… ………..…..8 ምዕራፍ ሶስት ............................................................................................................. 11 3. የአጠናን ዘዴ ......................................................................................................... 11

3.1 የናሙና አወሳሰድ ......................................................................................................................... 11 3.2 በጥናቱ የተካተቱ ተጠኝዎች .......................................................................................................... 12 3.3 የመረጃ አሰባሰብ ዘዴ .................................................................................................................... 14 3.4 የመረጃ አተናተን ዘዴ ................................................................................................................... 14 3.5 የመጠይቆች ምላሽ ነጥብ አሰጣጥ .................................................................................................. 14

ምዕራፍ አራት ............................................................................................................ 17 4. የጥናቱ ውጤት ትንተናና ማብራሪያ ........................................................................ 17

4.1 የጥናቱ ውጤት ............................................................................................................................. 17 4.1.1 ተቋማዊ ግምገማ ................................................................................................................... 17

4.1.1.1 አጠቃላይ ተቋማዊ ሁኔታ ...................................................................................................................17 4.1.1.2 የኢኮቴ መሳሪያዎች/አገልግሎት አቅርቦት ..........................................................................................19 4.1.1.3 የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን ....................................................................................20 4.1.1.4 ለኢኮቴ የተሰጠዉ ትኩረት.................................................................................................................21

4.1.2 በኢኮቴ ባለሙያዎች ደረጃ ግምገማ ....................................................................................... 22 4.1.2.1 የኢኮቴ ባለሙያዎች አጠቃላይ የግል ሁኔታ ......................................................................................22 4.1.2.2 የኢኮቴ ባለሙያዎች የኢኮቴ ዕዉቀት ............................................................................ 24 4.1.2.3 የባለሙያዎች የኢኮቴ አጠቃቀም ................................................................................... 25 4.1.2.4 የኢኮቴ ተፅዕኖ ................................................................................................................................26 4.1.2.5 ኮሪሊሽን .............................................................................................................................................28 4.1.2.6 የኢኮቴ ባለሙያ /የሂደት አስተባባሪ/ መምህራን አስተያየት ...............................................................29

4.1.3 በሰራተኛ ደረጃ ግምገማ ........................................................................................................ 29 4.1.3.1 አጠቃላይ የስራተኞች የግል ሁኔታ .....................................................................................................30 4.1.3.2 የኢኮቴ እውቀት .................................................................................................................................31 4.1.3.3 የኢኮቴ አጠቃቀም .............................................................................................................................32 4.1.3.4 የኢኮቴ ተፅዕኖ ...................................................................................................................................33 4.1.3.5 የሠራተኞች አስተያየት ......................................................................................................................35

4.1.4 በበላይ ሃላፊ ደረጃ ግምገማ ................................................................................................... 35 4.1.4.1 አጠቃላይ የበላይ ኃላፊዎች የግል ሁኔታ ............................................................................................36 4.1.4.2 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ ዕውቀት ......................................................................................................37 4.1.4.3 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ አጠቃቀም ..................................................................................................38 4.1.4.4 የኢኮቴ ተፅዕኖ በበላይ ኃላፊዎች እይታ.............................................................................................39 4.1.4.5 የበላይ ኃላፊዎች አስተያየት ...............................................................................................................40

4.1.5 በደንበኞች ደረጃ ግምገማ ...................................................................................................... 40 4.1.5.1 አጠቃላይ የግል ሁኔታ .......................................................................................................................41 4.1.5.2 የኢኮቴ ተፅዕኖ ...................................................................................................................................42

Page 9: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

4.2 የጥናቱ ውጤት ማብራሪያ ............................................................................................................. 43 4.2.1 ዝግጁነት............................................................................................................................... 45 4.2.2 አጠቃቀም ............................................................................................................................ 46 4.2.3 የኢኮቴ ተፅዕኖ ..................................................................................................................... 47 4.2.4 የዝግጁነት፣ አጠቃቀም እና ተፅዕኖ ኮሪሌሽን .......................................................................... 49

ምዕራፍ አምስት .......................................................................................................... 50

5. የጥናቱ ውጤት መደምደሚያና የመፍትሄ ሃሳብ........................................................ 50

5.1 የጥናቱ ውጤት መደምደሚያ ......................................................................................................... 50 5.2 የመፍትሄ ሃሳቦች .......................................................................................................................... 52

ዋቢዎች

አባሪዎች

Page 10: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

የሰንጠረዥ ማውጫ

ምዕራፍ ሶስት ............................................................................................................. 11 ሠንጠረዥ 1 የመጠይቆች ስርጭትና አመላለስ ...............................................................................................13 ሠንጠረዥ 2 ለትምህርት ደረጃ ነጥብ አሰጣጥ .................................................................................................15 ሠንጠረዥ 3 ለሥራ ልምድ ነጥብ አሰጣጥ ......................................................................................................15 ሠንጠረዥ 4 ለኢኮቴ ስልጠና ማስረጃ ነጥብ አሰጣጥ ......................................................................................15 ሠንጠረዥ 5 ለኢኮቴ ዕውቀት፣ አቅርቦትና ትኩረት ነጥብ አሰጣጥ ..................................................................15 ሠንጠረዥ 6 ለኢኮቴ ተጽዕኖ ነጥብ አሰጣጥ ...................................................................................................15 ሠንጠረዥ 7 ለኢኮቴ ባለሙያና ሰራተኞች የኢኮቴ አጠቃቀም ነጥብ አሰጣጥ ................................................16 ሠንጠረዥ 8 ለበላይ ኃላፊዎች ለኢኮቴ አጠቃቀም ነጥብ አሰጣጥ ...................................................................16 ሠንጠረዥ 9 ለኢኮቴ አገልግሎት ነጥብ አሰጣጥ .............................................................................................16

ምዕራፍ አራት ............................................................................................................ 17 ሠንጠረዥ 10 የኢኮቴ ተደራሽነት ሽፋን ......................................................................................................17 ሠንጠረዥ 11 የወረዳ ኔትና ስኩል ኔት ሽፋን .................................................................................................18 ሠንጠረዥ 12 የኢኮቴ መሳሪያዎች/ አገልግሎቶት አቅርቦት ...........................................................................19 ሠንጠረዥ 13 የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን ..........................................................................20 ሠንጠረዥ 14 ለኢኮቴ የተሰጠው ትኩረት ......................................................................................................21 ሠንጠረዥ 15 የኢኮቴ ባለሙያዎች አጠቃላይ መረጃ .....................................................................................23 ሠንጠረዥ 16 የኢኮቴ ባለሙያዎች የኢኮቴ ዕዉቀት ......................................................................................24 ሠንጠረዥ 17 የባለሙያዎች የኢኮቴ አጠቃቀም .............................................................................................25 ሠንጠረዥ 18 የኢኮቴ ተፅዕኖ በኢኮቴ ባለሙያዎች እይታ ............................................................................26 ሠንጠረዥ 19 የትምህርት ደረጃ፣ልምድና ስልጠና ኮሪሌሽን ............................................................................28 ሠንጠረዥ 20 የማይክሮሶፍት ወርድ ዕውቀት፣አጠቃቀምና ተጽዕኖ ኮሪሌሽን ..................................................29 ሠንጠረዥ 21 የኢኮቴ ባለሙያ /ሂደት አስተባባሪ/ አስተያየት ........................................................................29 ሠንጠረዥ 22 የሰራተኞች አጠቃላይ የግል ሁኔታ ..........................................................................................30 ሠንጠረዥ 23 የሰራተኞች የኢኮቴ ዕውቀት ....................................................................................................31 ሠንጠረዥ 24 የሰራተኞች የኢኮቴ አጠቃቀም ................................................................................................32 ሠንጠረዥ 25 የኢኮቴ ተፅዕኖ በሰራተኞች አይታ ...........................................................................................33 ሠንጠረዥ 26 የሠራተኛው አስተያየት ............................................................................................................35 ሠንጠረዥ 27 የበላይ ኃላፊዎች አጠቃላይ የግል ሁኔታ ..................................................................................36 ሠንጠረዥ 28 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ ዕውቀት ............................................................................................37 ሠንጠረዥ 29 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ አጠቃቀም ........................................................................................38 ሠንጠረዥ 30 የኢኮቴ ተፅዕኖ በበላይ ኃላፊዎች እይታ ..................................................................................39 ሠንጠረዥ 31 የበላይ ኃላፊዎች አስተያየት.....................................................................................................40 ሠንጠረዥ 32 የደንበኞች አጠቃላይ የግል ሁኔታ ............................................................................................41 ሠንጠረዥ 33 የኢኮቴ ተፅዕኖ በደንበኞች እይታ ............................................................................................42 ሠንጠረዥ 34 የኢኮቴ ተጽዕኖ በመንግስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እይታ .................................................47

Page 11: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

1

ምዕራፍ አንድ

1. መግቢያ

ዘመኑ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ሆኗል፡፡ የሰው ልጅ ቦታና ጊዜ

ሳይገድበው የሚፈልገውን በምስልና ድምጽ የተደገፈ መረጃ በፍጥነት ለመለዋወጥ ችሏል፡፡

ቴክኖሎጅው በፍጥነት በማደግ ላይ ከመሆኑም በተጨማሪ የሁሉንም ትኩረት እየሳበ

እንዲሁም በቀላሉና በአጭር ጊዜ ተቀባይነትን እያገኘ መጥቷል፡፡ በአጠቃላይ

የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዘርፈ ብዙ አገልግሎትና ጠቀሜታ ያለው

ከመሆኑም ባሻገር ለሰው ልጅ የእለት ከእለት የህይወት እንቅስቃሴ መሰረታዊ መሳሪያ

እየሆነ መጥቷል ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ለመገናኛ መሳሪያዎችና ለሌሎች በርካታ

አገልግሎቶች የተሰጠ ሥያሜ ነው፡፡ በስሩ ከሚካተቱ ዘርፎች መካከልም

ሬዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ ስልክ፣ኢንተርኔት፣ ኮምፒዩተርና ተያያዥ ጉዳዮች፣ ሳተላይትና

የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡ እንደ ቪዲዮ ኮንፈረንስ አይነት አገልግሎቶችም ዘርፉ ሲነሳ

አብረው የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዘርፈ ብዙ

አገልግሎቶችን ስለሚያካትት በየአገልግሎቶቹ አውድ እየነጣጠሉ መመልከት ይቻላል፡፡

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ከትምህርት፣ከጤና፣ ከግብርና እና ከሌሎችም

ዘርፎች አንፃር የሚሰጠዉን ጠቀሜታና የአጠቃቀም ሂደቱን ብንመለከት እንደ ዘርፎቹ

አይነት ጥቅም ላይ የሚዉልበት መንገድ ይለያያል፣ ለአገልግሎት የሚጠቀምባቸዉ

መሳሪያዎችም እንዲሁ እንደ አገልግሎቱ አይነትና ስፋት ይለያያሉ፡፡

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በሁሉም ዘርፎች መረጃ የመስጠትና የመቀበል

ሂደትን በማሳለጥ አስተማማኝና ፈጣን መረጃዎችን ለመለዋወጥ የሚያበረክተዉን አስተዋጽ

መገመት ይቻላል፤ ከዚህ አንፃር ደግሞ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ዉጤታማ

ለማድረግ የራሱ ሚና ይኖረዋል፡፡መንግስት ለህዝብ የሚሰጠዉን አገልግሎት ዘመናዊና

ቀልጣፋ ለማድረግ የአገልግሎት ሰጭ ተቋማትን አቅም ማሳደግ ቅድሚያ የሚሰጠዉ ጉዳይ

ነው፤ የተቋማት አቅም ማሳደጊያና ለአገልግሎት አሠጣጥ መሳለጥ ከሚረዱ ዋና ዋና

መንገዶች ዉስጥም ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነዉ፡፡

Page 12: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

2

መንግስት ዘርፉን ለአገልግሎት አሠጣጡ አጋዥ አድርጎ መጠቀሙ የዜጎችን ሁለንተናዊ

ተሳትፎ ከማሳደጉም ባሻገር የታቀዱ ተግባራትን ዉጤታማ በሆነ አፈፃፀም ለማከናወን

ያስችለዋል፡፡ ይህንንም በመረዳት የሃገሪቱ እንዲሁም የክልሉ መንግስት ኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን በመጠቀም ላይ ይገኛል፡፡ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጅ በክልላችን አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ በጥናት ማረጋገጥ

በርካታ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በመሆኑም የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ልማት ኤጀንሲ ከበርካታ የዘርፉ አይነቶች

መካከል በወረዳኔት፣ ኢንተርኔት፣ ስኩልኔት፣ መሰረታዊ ኮምፒዩተር አጠቃቀም እንዲሁም

በለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታቤዞች አጠቃቀም ላይ አተኩሮ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ

የመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶች ላይ የዳሰሳ ጥናት አካሂዷል፡፡ የዳሰሳ ጥናቱ ከክልሉ

ሁሉም አካባቢዎች በተመረጡ የክልል፣ ዞን፣ ከተማ አስተዳደርና ወረዳ ሴክተር መስሪያ

ቤቶች ላይ ‹‹በአማራ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጽዕኖ›› በሚል ርዕስ የተካሄደ ነው፡፡

ይህ የጥናት ሪፖርት አምስት ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በምዕራፍ አንድ መግቢያ፣ በምዕራፍ

ሁለት የተዛማጅ ጽሁፎች ክለሳ፣ በምዕራፍ ሶስት የአጠናን ዘዴ፣ በምዕራፍ አራት የጥናቱ

ውጤት ትንተናና ማብራሪያ፣ በምዕራፍ አምስት ደግሞ የጥናቱ ውጤት መደምደሚያና

የመፍትሄ ሃሳብ ይዟል፡፡ በተጨማሪም ዋቢዎችንና አባሪዎችን አካቷል፡፡

1.1 የጥናቱ ዳራ

በአገራችን ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን (ኢኮቴ)ን በመጠቀም በኩል አመታት

የተቆጠሩ ቢሆንም በሚፈለገው ደረጃ ዜጎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል ለማለት

አያስደፍርም፡፡ በመሆኑም መንግስት ዜጎችን የቴክኖሎጅ ተጠቃሚ ለማድረግና ኢኮቴ

የልማትና መልካም አስተዳደር ስርዓት ግንባታውን ለማሳለጥ እንዲያግዝ ለማስቻል

በፌዴራል ደረጃ ብሄራዊ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ (መመቴ) ፖሊሲና ስትራቴጅ

አውጥቶ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

በአማራ ክልልም ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን ጥቅም ላይ በማዋል በኩል

በክልሉ መንግስት እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ አበረታች ቢሆንም አብዛኛው የህብረተሰብ

ክፍል የእለት ከእለት ህይዎቱን ለመምራት ቴክኖሎጂውን መሳሪያው አድርጎ እየተጠቀመ

Page 13: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

3

አይደለም፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ደግሞ በክልላችን የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጅን እንቅስቃሴ የሚያስተባብርና የሚመራ አካል በተለያዩ አደረጃጀቶች ውስጥ

አልፏል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1995 ዓ.ም በክልላችን በአንድ ባለሙያና የሚመለከታቸውን

የክልል ቢሮዎች በኮሚቴ በማደራጀት ተጀመረ፡፡ ከዚያም በ1996 ዓ.ም የኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ማስፋፊያ ማዕከል በዩኒት ደረጃ ተጠሪነቱ ለአቅም ግንባታ ቢሮ

ሆኖ ተቋቋመ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያለ ከ2001 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ መሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ጥናት

ተጀምሮ የተለያዩ ማሻሻያዎች ሲደረጉበት ከቆየ በኋላ አሁን የያዘውን ቅርጽ ይዞ በሶስት

ዋና የስራ ሂደቶችና በሌሎች ደጋፊ የስራ ሂደቶች ተደራጅቷል፡፡

የክልሉ አስፈጻሚ አካል ከኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ጋር በተያያዘ በክልሉ

ውስጥ የሚከናወኑትን ተግባራት በበላይነት እንዲመራና እንዲያስተባብር በታህሳስ ወር

2002 ዓ.ም በደንብ ቁጥር 72/2002 የአብክመ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ

ልማት ኤጀንሲ በሚል ራሱን ችሎ እንዲቋቋም አድርጓል፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ልማት

ኤጀንሲ ራሱን ችሎ ከተቋቋመበት በኋላም ሆነ በፊት ከላይ በተጠቀሱት ባለፈባቸው

ደረጃዎች በርካታ ተግባራትን በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዙሪያ በማከናወን

ላይ ይገኛል፡፡ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከልም የወረዳ ኔትና ስኩል ኔት

እንቅስቃሴን መከታተል፣የሶፍትዌር ልማትና አስተዳደራቸውን መከታተል፣

በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዙሪያ ስልጠና መስጠትና ሌሎችም ተግባራት

በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ወረዳ ኔትን ከማስፋፋት አንጻር እስካሁን በክልሉ ውሥጥ 118

ያህል ወረዳዎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሲሆኑ ሌሎች 22 አዳዲስ ወረዳዎችና ሁለት

የመንግስት ተቋማት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ 269 ያህል

የሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች ደግሞ የስኩል ኔት አገልግሎት በመጠቀም

ላይ ይገኛሉ፤ በተለያዩ አካላት ሶፍትዌሮችና ድረ ገጾችም ለምተው በክልሉ አገልግሎት

በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ ኤጀንሲው እስካሁን በክልሉ ውስጥ በርካታ የኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ቁሳቁሶችን ለተለያዩ አካላት ያሰራጨ ሲሆን በተለይም የማህበረሰብ

ሁለገብ መረጃ ማዕከላትና በማቋቋምና በማጠናከር በኩል ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ

ነው፡፡

Page 14: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

4

የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ ፖሊሲና ስትራቴጅ (ነሀሴ 2001 ዓ.ም) የመረጃና መገናኛ

ቴክኖሎጅ የመልካም አስተዳደር ስርዓት ግንባታ ሂደትን እንደሚያግዝ በግልጽ

አስቀምጧል፡፡ ከስትራቴጅዉ የትግበራ መስኮች ዉስጥ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ አንደኛዉ

ነዉ፡፡

የክልላችን የኢኮቴ ልማት ኤጀንሲ ማቋቋሚያ ደንብም (ታህሳስ 2002 ዓ.ም) ለክልሉ

ሁለንተናዊ ልማት መፋጠንና መልካም አስተዳደር መጎልበት በዕዉቀትና መረጃ ላይ

የተመሰረተ አንድ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑንና በክልሉ

የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን በማልማትና በማስፋፋት ሴክተሮች ለህዝብና

መንግስት በቂ፣ ወቅታዊና ጥራት ያለዉ መረጃ በማግኘት የአገልግሎት አሰጣጣቸዉን

በጥራትና በፍጥነት ለማቅረብ እንደሚያስችላቸው ያትታል፡፡

ዶ/ር ሙቱክሪሽናን እና ሌሎች (ዲሴምበር 2009 እ.ኤ.አ.) ግልጽነት ያለዉ የመንግስት

መረጃ ስርዓትና አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር የመንግስትን አሰራር በኢኮቴ የተደገፈ

ማድረግ ወሳኝ እንደሆነ ያስቀምጣሉ፡፡ ጀርመን አገር የሚገኘዉ የሲገን ዩኒቨርሲቲ

(አፕሪል 2010 እ.ኤ.አ) ባስጠናዉ ጥናት በኢኮቴ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ የሰራተኞችን

የስራ ተነሳሽነት እንደሚጨምር አረጋግጧል፡፡ ባትናግር (ጁላይ 2001 እ.ኤ.አ.) ደግሞ

ለኢኮቴ ዘርፍ የተሻለ መዋዕለ ንዋይ ያፈሰሱ መንግስታት አገልግሎት አሰጣጣቸዉን

ማሻሻላቸዉን ይናገራሉ፡፡ በተለይ ኢንተርኔት በዚህ ረገድ ቀዳሚ ሚና አለዉ ብሏል፡፡

ሮቢን (ጁላይ 2004 እ.ኤ.አ.) ደግሞ በርካታ መንግስታት ኢኮቴን በመጠቀማቸዉ

የአገልግሎት አሰጣጡን ጥራት፣ ቅልጥፍና፣ ዉጤታማነትና ብቃት አሻሽሏል ይላል፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት ጽሁፎች በአጠቃላይ ኢኮቴ ለመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል

ምክንያት እንደሚሆን ያረጋግጣሉ፡፡

በሃገር ደረጃ በተለያየ ጊዜ የተነደፉ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ስትራቴጅዎችና ፖሊሲዎች፣

በክልላችንም የወጡ መመሪያዎችና ደንቦች፣ የተከናወኑ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሞች

በክልላችን በሚገኙ መ/ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሻሻል ያበረከቱት የራሳቸዉ ድርሻ

አላቸዉ፡፡ በዚህ ዙሪያ በርካታ ጉዳዮችን ማንሳት ይቻላል፡፡ ነገር ግን የኢኮቴ ድርሻን

ለብቻዉ ነጥሎ በክልላችን የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደሩትን ተፅዕኖ

መገመት ቢቻልም ሳይንሳዊ መንገድን የተከተሉ ጥናቶችም ማድረግ ጠቀሜታዉ የጎላ

ነዉ፡፡ በተለይ የአብክመ ኢኮቴ ልማት ኤጀንሲ ከተቋቋመበት ጀምሮ በኢኮቴ ምክንያት

Page 15: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

5

የክልላችን የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ተሻሽሏል ወይም አኮቴ በመንግስት አገልግሎት

አሰጣጥ ላይ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል ለማለት የሚያስችል ጥናት

በማከናወን የክልሉ መንግስት ለኢኮቴ የሚመድበዉ በጀት በትክክል ለታቀደለት አላማ

መዋሉን (Return on ICT investment) ማወቅ ይቻላል፡፡

በመሆኑም የመንግስት ተቋማት ለህዝብ በሚሰጡት አገልግሎት ላይ የኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል ለማወቅ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት

ለማካሄድ አራት አባላትን ያቀፈ አንድ የጥናት ቡድን ተቋቁሞ ይህን የዳሰሳ ጥናት

አካሂዷል፡፡

1.2 የጥናቱ መነሻ ሃሳብ

ምንም እንኳን የአንድ አገር መንግስት ለህዝብ የሚሰጠው አገልግሎት በኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መታገዙ ለተገልጋዩ የተቀላጠፈና ውጤታማ አገልግሎትን

ለማድረስ ጠቃሚ ቢሆንም በጉዳዩ ላይ የዘርፉ ተጽዕኖ ከአገር አገር እንዲሁም ከክልል

ክልል ይለያያል፡፡

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ብሄራዊ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ

ፖሊሲና ስትራቴጅ እንደተቀመጠው የኢትዮጵያ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ ፖሊሲ

(ነሃሴ 2001 ዓ.ም) የአገሪቱ አጠቃላይ የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ዓላማዎችና ግቦች አንዱ

መሰረታዊ አካል ነው፡፡ ይህ አገራዊ ፖሊሲ ለአገሪቱ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ ልማት

መሳካት ስትራቴጅያዊ ፋይዳ ይኖራቸዋል ተብለው ከሚታሰቡት ጉዳዮች መካከል

መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ ለመንግስት አስተዳደር በተለያዩ ዘርፎች የሚኖረውን ፋይዳ

የሚመለከተው አንዱ ነው፡፡ ፖሊሲው እንዳስቀመጠው መንግስት አግባብ ያላቸው

ስትራቴጅዎችን በመከተል የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ አጠቃቀም በህዝብና በመንግስት

አገልግሎቶች ውሥጥ ለመስፋፋትና ለማጠናከር የሚከተለውን አላማ ነድፏል፡፡

አላማውም ‹‹የኤሌክትሮኒክስ መንግስት ስርዓትን በመተግበርና በመጠቀም የህዝብ

አስተዳደር ዘርፍን ዘመናዊ በማድረግ ውጤታማና ብቃት ያለው የመንግስት አገልግሎት

አሰጣጥ እንዲሰፍን ማድረግ›› የሚል ነው፡፡

ከአገራዊ ፖሊሲው በተጨማሪ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ልማት ኤጀንሲ ማቋቋሚያ ደንብ (ታህሳስ 2002 ዓ.ም) ላይ

Page 16: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

6

እንዳስቀመጠው የኤጀንሲው መቋቋም አንዱ አላማ ‹‹የክልሉን መንግስታዊ ተቋማት እርስ

በእርስ አስተሳስሮ ቀጣይነት ባለው መንገድ ኦቶሜት ማድረግ፣ ከሰለጠነው ዓለም ጋር

እኩል የሚያራምድ ዘመናዊና አስተማማኝ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ

መሰረተ ልማት በመዘርጋት ቀልጣፋ የህዝብ አገልግሎት መስጠትና ለመልካም

አስተዳደር መስፈን ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከት›› የሚል ነው፡፡

ከላይ በአገራዊም ሆኑ በክልላዊ ሰነዶች የተጠቆሙትን ዓላማዎች ስኬት ለመገምገም

ሲባል በአማራ ክልል በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጂ ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

በተጨማሪም

መንግስት ለኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የሚመድበው ሃብት

በአግባቡ ለታቀደለት ዓላማ መዋሉንና ውጤታማነቱን ማረጋገጥ በማስፈለጉ

በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዙሪያ በክልሉ በቂ የሆነ ጥናትና

ምርምር ባለመደረጉ ዘርፉ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደረውን

ተፅዕኖ በተጨባጭ ለማወቅ ባለመቻሉ፤

በመሆኑም ‹‹ በአማራ ክልል በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ያሳደረው ተጽዕኖ ምን ይመስላል? ›› የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ

ጥናቱን ማካሄድ አስፈልጓል፡፡

1.3 የጥናቱ ዓላማ

የዳሰሳ ጥናቱ ዋና ዓላማ

በአማራ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጅ ያሳደረውን ተጽዕኖ መዳሰስ ነው፡፡

ዝርዝር ዓላማዎቹ፡-

የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ቁሳቁሶችና መሰረተ ልማት አቅርቦቶች

ለቀልጣፋና ውጤታማ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ

መዳሰስ

Page 17: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

7

ኢንተርኔት፣ ስኩልኔትና ወረዳኔት በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደሩትን

ተጽዕኖ መገምገም

የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታቤዞች በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደሩትን

ተጽዕኖ መቃኘት

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በአገልግሎት ሰጭ ሰራተኞች የስራ

ተነሳሽነትና የሥራ አፈፃፀም ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ መዳሰስ

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን ለመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ እንደ

አንድ መሳሪያ የመጠቀም አዝማሚያ ምን እንደሚመስል መቃኘት

የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን የተሳለጠ ለማድረግ ከኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጅ አንጻር የትኩረት አቅጣጫዎችን ማመላከት

1.4 የጥናቱ ወሰን

ይህ ጥናት የሚሸፍነው በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል፣ ዞንና ወረዳ የሚገኙ

የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ነው፡፡ በጥናቱ በክልል፣ በዞንና ወረዳ ደረጃ ከሚገኙ

የመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ወካይ ናሙናዎችን በመምረጥ በመላ የክልሉ

የመንግስት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጅ ያሳደረው ተጽዕኖ ተዳስሷል፡፡ በኢኮቴ ዘርፍ ያለውን ወሰን ስንመለከት ጥናቱ

የሚካሄደው በኮምፒውተር አጠቃቀም፣ በLAN መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በኢንተርኔት፣

በወረዳኔት፣ በስኩልኔት፣ በለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታቤዞች እንዲሁም በድረ ገጽ ዙሪያ ነው፡፡

1.5 የጥናቱ ውስንነት

ጥናቱ የሚከተሉት ውስንነቶች ነበሩበት፤ እነርሱም፡-

o ለጥናት በተመረጠው ርዕስ በተለይም በክልል ደረጃ በዘርፉ የተጠኑ በቂ ጥናቶች

አለመኖር፤

o የኢኮቴ ባለሙያዎች በዞንና በወረዳ ደረጃ በጥናቱ በታሰበው ናሙና ያህል ባለመገኘቱ

በርካታ መጠይቅ ተሞልቶ አለመመለሱ፤

o የተጠኝ ተቋማትን የበላይ ሃላፊዎች አግኝቶ መጠይቁን አለማስሞላት፤ በምትኩ በርካታ

የበላይ ሃላፊዎች መጠይቁን በተወካዮቻቸው ማስሞላት፡፡

Page 18: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

8

ምዕራፍ ሁለት

2. የተዛማጅ ጽሁፎች ክለሳ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ብሄራዊ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ

ፖሊሲና ስትራቴጅ (ነሃሴ 2001 ዓ.ም) እንደሚያትተው መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ

በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ላለው የዲሞክራሲና የመላካም አስተዳደር ስርዓት ግንባታ

ሂደት ያግዛል፡፡ ዋና ዋና የመመቴክ የትግበራ መስኮች በዲሞክራሲያዊ አስተዳደር ዙሪያ

እንደ ሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ፣ የፍትህ ስርዓት ማሻሻያ እና ያልተማከለ የአስተዳደር

ስርዓትን ወዘተ ያጠቃልላል፡፡ መመቴክ ሁሉም ዜጎች በፖለቲካዊ ሂደት እንዲሳተፉ

እንደዚሁም ከአለም አቀፍ ዕውቀትና የመረጃ ፍሰት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል በመስጠት

ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እንዲጠናከር ይረዳል፡፡ ስለሆነም መንግስት የዘላቂ ልማትና

ድህነት ቅነሳ እንደዚሁም የመልካም አስተዳደርና የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደቱን

ለማጠናከር የመመቴክን ልማት የማቀላጠፍ ቁርጠኝነት አለው፡፡

በተጨማሪም በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ

ልማት ኤጀንሲ ማቋቋሚያ ደንብ (ታህሳስ 2002 ዓ.ም) ኤጀንሲውን ማቋቋም ያስፈለገበትን

ምክንያት ከመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ አንጻር በክልሉ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጅን በማልማትና በማስፋፋት ሴክተሮች፣ ህዝብና መንግስት በቂ፣ ወቅታዊና ጥራት

ያለው መረጃ በማግኘት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን በጥራትና በፍጥነት ማቅረብ እንዲችሉ

እንዲሁም አስተማማኝ የሆነ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መሰረተ ልማት

በመዘርጋት ለክልሉ ሁለንተናዊ ልማት መፋጠንና ለመልካም አስተዳደር መጎልበት

በዕውቀትና መረጃ ላይ የተመሰረተ አንድ ኢኮኖሚያዊ ማህበረሰብ መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ

በመገኘቱ መሆኑ ተገልጧል፡፡

ዶ/ር ሙቱክሪሽናን እና ሌሎች (ዲሴምበር 2009 እ.ኤ.አ) ኢትዮጵያ በትኩረት እየሰራች

ያለው የመንግስት አስተዳደርን በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የተደገፈ የማድረግ

ሽግግር የዜጎቿን አስተዳደራዊ ተሳትፎ የሚያሳድግ ከመሆኑም በተጨማሪ ግልጽነት ያለው

የመንግስት የመረጃ ስርዓትና አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር ያደርጋል ይላሉ፡፡በተመሣሣይ

ጀርመን የሚገኘው የሲገን ዩኒቨርሲቲ በ 2010 እ.ኤ.አ. ባካሄደው ጥናት ባለንበት ዘመን

Page 19: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

9

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በሁሉም የስራ መስኮች በቀጥታም ይሁን

በተዘዋዋሪ አስፈላጊነቱ የጎላ ነው፡፡ በኢኮቴ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ በየጊዜው መሻሻል

ከማሳየቱም ባሻገር የሰራተኞችን የስራ ተነሳሽነት እንደሚጨምር አመልክቷል፡፡

ፍቅሬ (አፕሪል 2004 እ.ኤ.አ.) አማራ ክልል ላይ ባደረገው ጥናት ኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማፋጠንና ድህነትን ለመቀነስ

አይነተኛ መንገድ ነው ይላል፡፡ በአማራ ክልል ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂን

አስመልክቶ በተደረገ ጥናት ከተጠኝዎቹ ለመረዳት እንደተቻለው በክልሉ የሚካሄደውን

ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማፋጠንና ሁለንተናዊ ልማትን ለማምጣት ቴክኖሎጅው

ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡

በተጨማሪም ባትናግር (ጁላይ 2007 እ.ኤ.አ.) እንደሚለው መንግስታት ኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂን ከሌሎች ተግባራት ጋር አቀናጅተው መጠቀማቸውና ለዘርፉ

ልማትም መዋዕለ ነዋያቸውን ማፍሰሳቸው አስተዳደራቸውንና ለህዝብ የሚሰጡትን

አገልግሎት ለማሻሻል ያግዛቸዋል፡፡ የኢንተርኔትና ሌሎች ቴክኖሎጂዎች በፍጥነት ማደግ

ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂን በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቀዳሚ ሚና

እንዲኖረው አስችሏል፡፡

ሮቢን (ጁላይ 2011 እ.ኤ.አ) እንዳለው አዳዲስ ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ፣ ማስፋፋትና

በህብረተሰቡ ውስጥ እንዲሰርፅ ማድረግ እንዲህ በቀላሉ የሚቻል (Straight forward)

አይደለም፤ የራሱ የሆነ መሰናክሎች አሉት፤ ቢሆንም ባለፉት ዓመታት በርካታ አገራት

ኢኮቴን በመጠቀማቸው በህብረተሰቡ ዘንድ ቴክኖሎጂው ተፈላጊና ተቀባይነት እንዲያገኝ

ሆኗል፡፡ የአገልግሎት አሠጣጡንም ጥራት፣ ቅልጥፍና ውጤታማነትና ብቃት በማሻሻሉ “

ብርማው ጥይት” (Silver Bullet) እስከ መባል ደርሷል፡፡ እንደሮቢን ገለፃ ኢኮቴ

ለአገልግሎት አሰጣጥ ስኬት የሚያበረክተውን ድርሻ በሶስት ደረጃ ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡

እነርሱም ዝግጁነት (Readiness)፣ አጠቃቀም (Use) እና ተፅዕኖ (Impact) ናቸው፡፡ እነዚህ

ሶስቱ አወንታዊ ግንኙነት አላቸው፡፡ ዝግጁነት የቴሌ ኮም መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣የኢኮቴ

እውቀትን ወዘተ. ሲያካትት በአጠቃላይ የአጠቃቀም ቅድመ ሁኔታን ያመለክታል፡፡

ተጽዕኖ ደግሞ የኢኮቴ ተደራሽነት በማግኘት፣ የኢኮቴ እውቀት በመኖርና ኢኮቴን

በተደጋጋሚ በመጠቀም የሚገኝ ውጤት እንደሆነ ያብራራል፡፡ የአገልግሎት ጥራትንና

Page 20: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

10

ፍጥነትን የማሻሻል የመንግስት ወጭን የመቆጠብ ወዘተ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ ኢኮቴ

ለአገልግሎት አሰጣጡ ተጽዕኖ እንዲያሳድር ከዝግጁነትና አጠቃቀም ጋር የተዛመዱ

ስራዎችን መስራት ይገባል፡፡ እነዚህ እርስ በእርሳቸው ተያያዥነትና ትስስር አላቸው፡፡

መንግስት የቀጥታ መስመር አገልግሎትን (Online Service Provision) ለህዝቡ አካባቢው

ድረስ ሲያቀርብ ተገልጋዩ በአጸፋው በአገልግሎቱ ከመርካት አንስቶ በልማት ተሳታፊ

እንዲሆን ያደርጋል፤ በተጨማሪም ለመንግስት ያለው አመኔታ (Trust) ይጨምራል እንደ

ሮቢን ሃተታ፡፡

ከላይ የተጠቀሱ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ

ለአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናና ለተፋጠነ ልማት አስተዋፅኦው የጎላ ነው፡፡ መንግስት

ለህዝብ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ግልጽ፣ አሳታፊና ቀልጣፋ ለማድረግ ቴክኖሎጅውን

መጠቀም አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ዘርፍ የተካሄዱ ጥናቶች በርካታ የሚባሉ

ባይሆኑም የጥናት ቡድኑ ከላይ ያሉትን ከጥናት ርዕሱ ጋር የሚዛመዱ ሪፖርቶች በመዳሰስ

ለዳሰሳ ጥናቱ በአጋዥነት ተጠቅሞበታል፡፡ የዚህ ጥናት አስፈላጊነት በጥናቱ የተካተቱ

የኢኮቴ ዘርፎች በክልሉ ውስጥ አጠቃላይ ያሉበትን ደረጃ በማወቅ ለዕድገትና

ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሳካት ውጤታማ በሆነ መንገድ አገልግሎት ላይ የሚውሉበትን

ስልት ማመላከት ነው፡፡

Page 21: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

11

ምዕራፍ ሶስት

3. የአጠናን ዘዴ

የጥናቱ ስልት ጠቋሚ ወይም ቃኚ (Survey Study) ሲሆን ይህ የምርምር ስልት ችግሮችን

ወይም ሁኔታዎችን በጠቅላላ የሚዳስስና አጠቃላይ ግንዛቤ የሚሰጥ ነው፤ ጉዳዮችን

በጥልቀት አይመረምርም፡፡ ሆኖም ግን ሁኔታዎችን ወይም ችግሮቹን ወደፊት በጥልቀት

ለማጥናት ለሚፈልጉ ተመራማሪዎች ፍንጭ ይሰጣል፡፡ ይህንን የጥናት ስልት ማካሄድ

ተመራጭ የሚሆነው ከችግሮች አይነትና መጠን ጋር ለመተዋወቅና ጠለቅ ያለ ጥናት

ለማካሄድ የሚያስፈልጉ ስልቶችን ለመቀየስ ነው፡፡

3.1. የናሙና አወሳሰድ

ጥናቱ እኩል እድል የማይሰጥ የናሙና አወሳሰድ ዘዴን ተጠቅሟል፡፡ በጥናቱ ውስጥ

የተካተቱ ተጠኝዎች በዒላማ የናሙና አወሳሰድ ዘዴ (Purposeful Sampling Method)

የተመረጡ ናቸው፡፡ ይህ የናሙና አወሳሰድ ዘዴ ተመራማሪው አንዳንድ ተጠኝዎች

በጥናቱ ውስጥ ቢካተቱ የተሻለ መረጃ ለማግኘትና የምርምሩ ውጤት የበለጠ አስተማማኝ

እንዲሆን ይረዳል ብሎ ሲገምት ስራ ላይ የሚውል ዘዴ ሲሆን በናሙናው ውሥጥ

የሚካተቱት ሆን ተብሎ የሚመረጡ ተጠኝዎች ናቸው፡፡ ከዚህ ጥናት አንጻርም ይህን

የናሙና አመራረጥ ዘዴ መጠቀም የተፈለገበት ዋና ምክንያት ቴክኖሎጅው በክልሉ

የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ መቃኘት በመሆኑ ለህዝብ

ከሚሰጡት አገልግሎት አንጻር ቴክኖሎጅውን በመጠቀም ላይ ያሉና ወደፊትም ከተያዙ

ፕሮጀክቶች አንጻር ቴክኖሎጂውን ሊጠቀሙ የሚችሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን መርጦ

ለማካተት ስለሚያስችል ነው፡፡ ወረዳዎች ላይ ያለው የናሙና አመራረጥ ሁኔታ ደግሞ

በጥናቱ የተመረጡ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዘርፎች በክልሉ ውሥጥ

በየአስተዳደር እርከኑ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያላቸውን ተጽዕኖ ለመዳሰስ

በጥናት ኮሚቴው እይታ የክልሉን ገጽታ እንዲወክሉ በማሰብ ከገጠርም ከከተማም

ወረዳዎች ተቀላቅለው የተመረጡ ናቸው፡፡

Page 22: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

12

3.2. በጥናቱ የተካተቱ ተጠኝዎች

I. በክልል ደረጃ ከሚገኙ መስሪያ ቤቶች አስራ አምስቱን በመምረጥ

ከእያንዳንዱ መስሪያ ቤት አስር አስር ተጠኝዎች በጠቅላላው 150

ተጠኝዎች ተመርጠዋል፡፡ የእነዚህ ተጠኝዎች ድርሻም በእያንዳንዱ መስሪያ

ቤት 2 የተቋሙ የበላይ ሃላፊዎች፣ 2 የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን

ቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ 4 የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች እና 2 የመስሪያ ቤቱ

ደንበኞች ነው፡፡

II. በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ሁሉንም የዞን አስተዳደሮች በማካተት ከእያንዳንዱ

ዞን አስር አስር የዞን መምሪያዎችን ተመርጠዋል፤ ከእያንዳንዱ የተመረጠ

መምሪያ አምስት አምስት ተጠኝዎች ተመርጠው በአንድ ዞን በአጠቃላይ 50

ተጠኝዎች ተካተዋል፡፡ በአጠቃላይ በአስሩ ዞኖች 500 ተጠኝዎች

ተካተዋል፡፡ የእነዚህ ተጠኝዎች ዝርዝር ድርሻም 1 የመምሪያው የበላይ

ሃላፊ፣ 1 የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ፣ 2 ሰራተኞች

እና 1 የመስሪያ ቤቱ ደንበኛ ነው፡፡

III. ሶስቱ ታላላቅ ከተማ አስተዳደሮች በጥናቱ የተካተቱ ሲሆን ከእያንዳንዱ

ከተማ አስተዳደር አስር አስር መስሪያ ቤቶች ተካተዋል፤ ከእያንዳንዱ

የተመረጠ መስሪያ ቤት ደግሞ አምስት አምስት ተጠኝዎች ተመርጠው

በአንድ ከተማ አስተዳደር በአጠቃላይ 50 ተጠኝዎች ፣ በአጠቃላይ በሶስቱ

ከተማ አስተዳደሮች 150 ተጠኝዎች ተካተዋል፡፡ የተጠኝዎች ድርሻ 1

የመስሪያ ቤቱ የበላይ ሃላፊ፣ 1 የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ

ባለሙያ፣ 2 ሰራተኞች እና 1 ደንበኛ ነው፡፡

IV. ከሁሉም ዞን አስተዳደሮች በአጠቃላይ 34 የገጠር ወረዳዎች እና ከተማ

አስተዳደሮች በጥናቱ ተካተዋል፡፡ እነዚህ የገጠር ወረዳዎችና ከተማ

አስተዳደሮች ደግሞ ዞኑ እንዳቀፋቸው ወረዳዎች ብዛት ድርሻቸው ተሰልቶ

በአንድ ዞን ከ2 እስከ 4 ወረዳዎች ተመርጠዋል፤ ከእያንዳንዱ የተመረጠ

ወረዳ/ከተማ አስተዳደር ደግሞ አራት አራት ጽ/ቤቶች ተመርጠው

ተካተዋል፡፡ ከተመረጡ አራት ጽ/ቤቶች እያንዳንዳቸው አራት አራት

ጠቅላላ ከአንድ ወረዳ 16 ተጠኝዎች ተካተዋል፡፡ በአጠቃላይ ከሰላሳ አራት

ወረዳዎች 544 ተጠኝዎች ተመርጠው ተካተዋል፡፡ የእነዚህ ተጠኝዎች

Page 23: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

13

ድርሻም በእያንዳንዱ ጽ/ቤት 1 የጽ/ቤቱ የበላይ ሃላፊ፣ 1 የኢንፎርሜሽንና

ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ፣ 1 ሰራተኛ እና 1 ደንበኛ ነው፡፡

V. በጥናቱ ውስጥ የተካተቱ ተጠኝዎች በሁሉም ደረጃ የሚገኙ

የመስሪያ ቤቱ ደንበኞች፣

የኢኮቴ ባለሙያዎች ወይም የስራ ሂደት ባለቤቶች፣

የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች፣

የተቋሙ የበላይ ሃላፊዎች ናቸው፡፡

በአጠቃላይ በጥናቱ ከሁሉም ምድቦች በድምሩ 1344 ተጠኝዎች ተካተዋል፡፡

የተሰራጨውና ተሞልቶ የተመለሰው የመጠይቅ ብዛትም እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሠንጠረዥ - 1 የመጠይቆች ስርጭትና አመላለስ

ተጠኝ

የተሰራጨ መጠይቅ ብዛት

ተሞልቶ የተመለሰ መጠይቅ ብዛት

መጠይቁን ሞልተው የመለሱ ተጠኝዎች

በጾታ

ተሞልቶ የተመለሰ መጠይቅ በፐርሰንት ወንድ ሴት

የኢኮቴ ባለሙያዎች ወይም የስራ ሂደት ባለቤቶች

296 200 150 50 67.57%

የመስሪያ ቤቱ ደንበኞች

296 246 190 56 83.1%

የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች

456 399 273 126 87.5%

የተቋሙ የበላይ ሃላፊዎች

296 245 207 38 82.77%

ድምር

1344 1090 820 270 81.1%

በጠቅላላው መጠይቁን ሞልተው ከመለሱ 1090 ተጠኝዎች መካከል ወንዶቹ 820 ሲሆኑ

ሴቶቹ ደግሞ 270 ናቸው፡፡

Page 24: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

14

3.3 የመረጃ አሰባሰብ ዘዴ

ጥናቱን ለማካሄድ ሁለት የመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች አገልግሎት ላይ የዋሉ ሲሆን ዋነኛው

ዘዴ መጠይቅ ነው፡፡ መጠይቁን በማዘጋጀትና ተጠኝዎችን በአካል በማግኘት ስለአሞላሉ

ገለጻ አድርጎ በማስሞላት መረጃው ተሰብስቧል፡፡ መጠይቁን በማስሞላት በኩል የዞንና

የወረዳ ኢኮቴ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል፡፡ የመስክ ምልከታ ሌላው የመረጃ

መሰብሰቢያ መሳሪያ ሲሆን የጥናት ቡድኑ የምልከታ ቼክ ሊስት በማዘጋጀት በጉብኝቱ

ወቅት የተስተዋሉ መረጃዎችን ሰብስቧል፡፡ በእነዚህ ሁለት የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች

በአጠቃላይ ለጥናቱ የሚያግዙ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡

3.4 የመረጃ አተናተን ዘዴ

በተለያየ መንገድ ከመስክ ምልከታና ከተጠኝዎች በመጠይቅ የተሰበሰቡ መረጃዎች SPSS

እና Microsoft Excel ሶፍትዌሮችን በመጠቀም ተጠናቅረዋል፤ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱን

ውጤት ለማሳየትም ጥምርታ (Ratio) ፣ መቶኛ (Percent) ፣ አማካይ (Mean) ፣

ስታንዳርድ ዲቬሽን (Standard Deviation) እንዲሁም ኮርሌሽን (Correlation) የተባሉት

ስታትስቲካዊ መለኪያዎች ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ከመረጃዎቹ ትንተና በኋላም ይህ

አጠቃላይ ሪፖርት ተዘጋጅቷል፡፡ በጥናቱ ውስጥ ቀልጣፋነት፣ ውጤታማነት፣ የደንበኞች

እርካታ፣ ግልጽነት እና ፍትሃዊነት፤ወጪ ጊዜና ውጣ ውረድን መቀነስና ተዛማጅ ጉዳዮች

በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ኢኮቴ ላሳደረው ተጽዕኖ አመልካቾች (Indicators)

ተደርደው ተወስደዋል፡፡

3.5. የመጠይቆች ምላሽ ነጥብ አሰጣጥ

መጠይቆቹን ለማዘጋጀትና የምላሾቹን ነጥብ ለመስጠት የተከተልነው ዘዴ የታዋቂውን

የሊከርት (Likert) ነጥብ አሰጣጥ ዘዴ ሲሆን በሁሉም መጠይቆች ክፍል 1 ላይ ጾታ፣

ዕድሜ፣ የመኖሪያ/የሥራ ቦታ ተመሳሳይ ነጥብ አላቸው፡፡ በአጠቃላይ የትምህርት ደረጃ፣

የሥራ ልምድ፣ የኢኮቴ/ተዛማጅ ሥልጠና ማስረጃ፣ የኢኮቴ አገልግሎት፣ የኢኮቴ ዕውቀት፣

የኢኮቴ አጠቃቀም እና የኢኮቴ ተፅዕኖ ደግሞ በሚከተሉት ሠንጠረዦች እንደተመለከተው

መጠይቆቹ ላይ በተሰጠው የምርጫ ተራ ቁጥር መሠረት ነጥብ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ለአብት

የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን ሁሉም ለሚሉት 4፣አብዛኛዉ 3 ፣ጥቂት 2

እና ምንም 1 ነጥብ ተሰጥቷቸዋል ፡፡

Page 25: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

15

ሠንጠረዥ 2 ለትምህርት ደረጃ ነጥብ አሰጣጥ

የትምህርት ደረጃ የተሰጠው ነጥብ

ሰርትፊኬትና በታች 1 ዲፕሎማ 2 የመጀመሪያ ዲግሪ 3 ሁለተኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ 4

ሠንጠረዥ 3 ለሥራ ልምድ ነጥብ አሰጣጥ

የሥራ ልምድ የተሰጠው ነጥብ ከ5 ዓመት በታች 1 5-10 2 11-15 3 ከ15 ዓመት በላይ 4

ሠንጠረዥ 4 ለኢኮቴ ስልጠና ማስረጃ ነጥብ አሰጣጥ የኢኮቴ/ተዛማጅ ስልጠና

ማስረጃ የተሰጠው ነጥብ

የለኝም 1 ሰርተፊኬት 2 ዲፕሎማ 3 ከዲፕሎማ በላይ 4

ሠንጠረዥ 5 ለኢኮቴ ዕውቀት፣አቅርቦትና ትኩረት ነጥብ አሰጣጥ

ሠንጠረዥ 6 ለኢኮቴ ተጽዕኖ ነጥብ አሰጣጥ

የኢኮቴ ተጽዕኖ የተሰጠው ነጥብ በጣም አልስማማም 1 አልስማማም 2 አላወኩም 3 እስማማለሁ 4 በጣም እስማማለሁ 5

ለኢኮቴ ዕውቀት፣ አቅርቦትና ትኩረት

የተሰጠው ነጥብ

ምንም 1 ዝቅተኛ 2 መካከለኛ 3 ከፍተኛ 4

Page 26: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

16

የኢኮቴ አጠቃቀምን ለሚመለከቱ ጥያቄዎች ለተሰጡ ምርጫዎች በባለሙያው ለሚሞላው

መጠይቅ አራት ነጥቦች ሲኖሩት በኃላፊዎች ለሚሞላው መጠይቅ ግን ትንሽ ዘርዘር

ተደርጎ አምስት ነጥቦች ተሰጥቶታል ፡፡

ሠንጠረዥ 7 ለኢኮቴ ባለሙያና ሰራተኞች የኢኮቴ አጠቃቀም ነጥብ አሰጣጥ የኢኮቴ አጠቃቀም የተሰጠው ነጥብ በጭራሽ 1 አንዳንድ ጊዜ 2 በተደጋጋሚ 3 ሁልጊዜ 4

ሠንጠረዥ 8 ለበላይ ኃላፊዎች ለኢኮቴ አጠቃቀም ነጥብ አሰጣጥ የኢኮቴ አጠቃቀም የተሰጠው ነጥብ በጭራሽ 1 አልፎ አልፎ 2 አንዳንድ ጊዜ 3 በተደጋጋሚ 4 በጣም በተደጋጋሚ

5

በሌላ በኩል የኢኮቴ አገልግሎት የት ያገኛሉ ለሚለው የመጠይቅ ክፍል ግን ከአንድ በላይ

መልስ ሊኖረው ስለሚችል በመልሱ የተሰጠውን ቅድመ ተከተል ሳይጠብቅ በሠንጠረዥ

እንደተመለከተው ተስተካክሎ ነጥብ ተሰጥቶታል ፡፡

ሠንጠረዥ 9 ለኢኮቴ አገልግሎት ነጥብ አሰጣጥ የኢኮቴ አገልግሎት የት ያገኛሉ? የተሰጠው

ነጥብ አላገኝም 1 በመንግስት ተቋማት 2 ኢንተርኔት ካፌና ሌሎች ተቋማት

3

መኖሪያ ቤቴ 4

Page 27: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

17

ምዕራፍ አራት

4. የጥናቱ ውጤት ትንተናና ማብራሪያ

በአጠቃላይ ይህ ምዕራፍ ስለ ዳሰሳ ጥናቱ ውጤት ያብራራል፡፡ በተዘጋጀው የጽሁፍ

መጠይቅ እንዲሁም በመስክ ምልከታ የተሰባሰቡ ጥሬ መረጃዎች

ተተንትነውበታል፤ትንተናው በሰንጠረዥ እና በሃተታ ስታትስቲካዊ በሆነ መንገድ

ተከናውኗል፡፡ የመረጃ ትንተናው የሚያስተላልፈው መልዕክትም እያንዳንዱን ሰንጠረዥ

መሰረት በማድረግ ተተንትኗል፡፡

4.1. የጥናቱ ውጤት በመጠይቁ የተሰበሰበውን መረጃ ለመተንተን SPSS ሶፍትዌርን የተጠቀምን ሲሆን

በምልከታ የተሰበሰበውን አሃዛዊ መረጃ ደግሞ MS Excel ተጠቅመናል፤ የመጠይቆቹን

ዓይነት መሠረት በማድረግ እና በአጠቃላይ ተጠኝውን ተቋም ለመዳሰስ ሲባል ትንተናው

በተቋም፣ በኢኮቴ ባለሙያ፣ በሠራተኛው፣ በበላይ ኃላፊ እና በደንበኛ ደረጃ ተከፋፍሎ

ተተንትኗል፡፡

4.1.1 ተቋማዊ ግምገማ ምልከታው የተደረገባቸው ተቋማት ብዛት 15 ክልል ቢሮዎች ፣ 100 ዞን መምሪያዎች ፣

30 የከተማ አስተዳደር ጽ/ቤቶች እና 136 የወረዳ ጽ/ቤቶች በድምሩ 281 ተቋማት

ናቸው፤ ነገር ግን የተሟላ መረጃ የተሰበሰበባቸው 252 ተቋማት ናቸው፡፡

4.1.1.1 አጠቃላይ ተቋማዊ ሁኔታ

ይህንን ትንተና ለማከናወን በመስክ ምልከታ የተገኘ ዳታ የተጠቀምን ሲሆን ለንጽጽር

እንዲረዳም በመጠይቅ የተገኘውን መረጃ ለማካተት ተሞክሯል፡፡

ሠንጠረዥ 10 የኢኮቴ ተደራሽነት ሽፋን

የምልከታ የተደረገባቸው የተቋም ብዛት

የሰው ኃይል ብዛት

የኮምፒውተር ብዛት

ኮምፒውተር- ሠራተኛ ጥምርታ

ኢንተርኔት አገልግሎት የሚያገኙ (ሽፋን)

LAN መሠረተ ልማት ዝርጋታ ያላቸው (ሽፋን)

የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች ያላቸው(ሽፋን)

ድረ-ገጽ ያላቸው (ሽፋን)

252 10613 3869 1 ፡ 3 116(46.03%)

105(42.2% ) 92(37.00%) 16(6.40%)

Page 28: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

18

ከላይ በሰንጠረዥ 10 እንደተመለከተው ምልከታ የተደረገባቸው 252 ተቋማት ሲሆኑ የሰው

ኃይል ብዛታቸውም በአጠቃላይ 10613 ነው፡፡ እነዚህ ተቋማት ያላቸው የኮምፒውተር

መጠን ( ዴስክ ቶፕና ላፕቶፕ ) 3869 ሲሆን በዚህ መሠረት ኮምፒውተር ሠራተኛ

ጥምርታው 1 ለ 3 ይሆናል፤ ይህ ማለት ከሶስት ሠራተኞች አንዱ ኮምፒውተር ይጠቀማል

ማለት ነው ፡፡ ከነዚህ ተቋማት ውስጥ 116ቱ የኢንተርኔት አገልግሎት፣ 105ቱ LAN

መሠረተ ልማት ፣ 92ቱ የለሙ ሶፍዌሮችና ዳታ ቤዞች እንዲሁም 16ቱ ብቻ የራሳቸው

ድረ ገጽ ያላቸው ናቸው፡፡ በዚህ መሠረት 46.03%፣ 42.20%፣ 37.00% እና 6.40%

የኢንተርኔት፣ የLAN መሠረተ ልማት፣ ሶፍትዌርና ዳታ ቤዝ እና ድረ ገጽ ሽፋን በቅደም

ተከተል እንዳላቸው እንረዳለን፡፡ ከተጠቀሱት አገልግሎቶች የኢንተርኔትና የLAN

መሠረተ ልማት ሽፋኖች የተሻሉ፣ የለሙ ሶፍዌሮችና ዳታ ቤዞች ሽፋን መጠነኛ ሲሆኑ

በተቃራኒው የድረ-ገጽ ሽፋን ዝቅተኛ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡

ሠንጠረዥ 11 - የወረዳ ኔትና ስኩል ኔት ሽፋን ምልከታ የተደረገባቸው ወረዳዎችና ከተማ አስ/ ብዛት

ወረዳኔት ያላቸው ወረዳዎች ብዛት

ስኩልኔት ያለባቸው ወረዳዎች ብዛት

የወረዳኔት ሽፋን በ%

የስኩልኔት ሽፋን በ%

34 33 33 97% 97%

ከላይ በሰንጠረዥ 11 እንደተመለከተው ምልከታ ከተደረገባቸው 34 ወረዳዎችና ከተማ

አስተዳደሮች ውሥጥ 33 (97%) የወረዳኔት አገልግሎት ተጠቃሚ ሲሆኑ በተመሳሳይ 33

(97%) የስኩል ኔት ተጠቃሚ ናቸው፡፡ ምልከታ ከተደረገባቸው ወረዳዎችና ከተማ

አስተዳደሮች መካከል በከተማ አስተዳደር ደረጃ የተቋቋሙት ራሳቸውን ችለው የወረዳኔት

መሰረተ ልማት አልተዘረጋላቸውም፤ ነገር ግን በሚገኙበት ከተማ ባለው የወረዳ አስተዳደር

መሰረተ ልማቱ በመኖሩና ሁሉንም የወረዳ ኔት አገልግሎቶች ከዚሁ ወረዳ አስተዳደር

ስለሚያገኙ የጥናት ቡድኑ መሰረተ ልማቱ እንዳላቸው ታሳቢ አድርጓል፤ ይህም በመሆኑ

የወረዳ ኔት ሽፋኑ ከፍ ብሎ 97% ለመድረስ ችሏል፡፡

Page 29: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

19

4.1.1.2 የኢኮቴ መሳሪያዎች/አገልግሎት አቅርቦት

ሠንጠረዥ 12 የኢኮቴ መሳሪያዎች/ አገልግሎቶት አቅርቦት

የኢኮቴ መሳሪያዎች /አገልግሎት አቅርቦት

የለም ዝቅተኛ መካከለኛ ከፍተኛ አማካይ

(Mean)

ሰታንዳርድ ዲቪየሽን (SD)

የኮምፒውተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሳሪያዎች

5.21% 41.67% 37.50% 15.62% 2.64 .81

የዲያላፕ፣ ብሮድ ባንድ፣ CDMA ኢንተርኔት አገልግሎት

39.58% 29.17% 17.71% 13.54% 2.05 1.06

የወረዳኔት ወይም የስኩል ኔት አገልግሎት

43.98% 26.18% 23.04% 6.81% 1.93 .97

የLAN መሠረተ ልማት ዝርጋታ 32.80% 34.39% 20.63% 12.17% 2.12 1.01 የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች 38.42% 32.11% 22.63% 6.84% 1.98 .94 የለማ ድረ-ገፅ 65.43% 24.47% 8.51% 1.60 % 1.46 .72 የባለቤትነት መብት ያላቸው አንቲቫይረሶች

47.64% 27.23% 15.71% 9.42% 1.87 1.00

ከላይ በሰንጠረዥ 12 እንደምንመለከተው የኢኮቴ መሳሪያዎች ወይም አገልግሎት

አቅርቦትን በተመለከተ ለኢኮቴ ባለሙያዎችና የሥራ ሂደት መሪዎች ከተሰራጨው

መጠይቅ በተገኘ ምላሽ ኮምፒውተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት ከፍተኛውን

ድርሻ (94.79%) ይይዛል፤ በመቀጠል የLAN መሠረተ ልማት ዝርጋታ እና የኢንተርኔት

አገልግሎት በቅደም ተከተል 67.19% እና 60.42 ሲሆኑ በጣም ዝቅተኛው አቅርቦት

34.58% የለማ ድረ-ገፅ መሆኑን እንረዳለን፡፡ በነጥብ አሰጣጣችን ምንም አቅርቦት ለሌለው

1፣ ለዝቅተኛ 2፣ ለመካከለኛ 3 እና ለከፍተኛ አቅርቦት 4 በመሆኑ የኮምፒውተርና ተዛማጅ

የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት አማካይ (Mean) 2.64 መሆኑ የሚያሳየን አቅርቦቱ

መካከለኛ መሆኑን ነው፤ በሌላ በኩል የLAN መሠረተ ልማት ዝርጋታና የኢንተርኔት

አገልግሎት በቅደም ተከተል 2.12 እና 2.05 መሆኑ የሚያሳየን የLAN መሰረተ ልማት

ዝርጋታ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ዝቅተኛ መሆኑን ነው፡፡ በተጨማሪም ዝቅተኛ

ስታንዳርድ ዲቪየሽን (SD) 0.72 ያለው የለማ ድረ ገጽ መሆኑ የሚያመለክተዉ

በተጠኝዎች ምላሽ መካከል ከአማካዩ ሠፊ ልዩነት አለመኖሩን እንረዳለን፡፡ በተቃራኒዉ

ከፍተኛ ስታንዳርድ ዲቬሽን (SD) 1.06 ያለዉ የኢንተርኔት አገልግሎት መሆኑ

በተጠኝዎች ምላሽ መካከል ከአማካዩ ሰፋ ያለ ልዩነት ያላቸዉ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡

Page 30: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

20

በሌላ በኩል የለማ ድረ ገጽ አማካይ 1.46 መሆኑ አቅርቦቱ እጅግ ዝቅተኛ መሆኑን

ያመለክታል፡፡ በአብዛኛዉ (65.43%) መላሾች የለማ ድረ ገጽ አለመኖሩን በመልሳቸው

አሳይተዋል፡፡ በአጠቃላይ ግን የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት በአማካይ ዝቅተኛ (1.58)

ነው፡፡

4.1.1.3. የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን

ሰንጠረዥ 13 የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን

ምንም ጥቂት አብዛኛዉ ሁሉም አማካይ (Mean)

ስታንዳርድ ዲቬዥን (SD)

ኮምፒዩተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሳሪያዎች ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን

2.56% 48.21% 43.59% 5.64% 2.52 0.64

ኢንተርኔት፣የወረዳኔት ወይም ስኩልኔት ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን

28.35% 54.64% 13.92% 3.09% 1.92 0.74

በ LAN መሰረተ ልማት የታገዘ አገልግሎት ሰጭ ሠራተኛ መጠን

36.27% 43.01% 17.62% 3.11% 1.88 0.81

የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች ተጠቃሚ ሠራተኛ ብዛት

28.87% 58.76% 11.86% .52% 1.8 0.64

የተቋሙን ድረ ገጽ ተጠቃሚ ሠራተኛ ብዛት

67.19% 22.92% 8.85% 1.04% 1.11 0.70

የቪዲዮ ኮንፈረንስ ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን

60.32% 29.63% 8.47% 1.59% 1.51 0.72

ከላይ በሰንጠረዥ 13 እንደተመለከተዉ ኮምፒዩተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሳሪያዎች

ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን ከፍተኛ ነዉ (97.44% ይሸፍናል)፡፡ በመቀጠል ኢንተርኔት፣

ስኩልኔት ወይም ወረዳ ኔት ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን 71.65%፣ የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ

ቤዞች ተጠቃሚ ሠራተኛ ብዛት 71.14%፣ በ LAN መሰረተ ልማት የታገዘ አገልግሎት

ሰጪ ሰራተኛ መጠን እና የድረ-ገጽ ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን በቅደም ተከተል 39.69%

እና 32.81% ናቸዉ፡፡ በአጠቃላይ የኮምፒዩተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሳሪያዎች ተጠቃሚ

ሰራተኛ መጠን አማካይ 2.52 መሆኑ አብዛኛዉ ተጠቃሚ መሆኑን ሲያመለክት ሌሎች

አገልግሎቶችን የሚጠቀሙ ሰራተኞች ግን ጥቂት ናቸዉ፡፡ ከነዚህ ዉስጥ የኢንተርኔት፣

ወረዳኔት ወይም ስኩልኔት ተገልጋይ ቁጥር በንጽጽር የተሻለ ተጠቃሚ አላቸዉ፡፡

Page 31: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

21

የተቋሙን ድረ ገጽ ግን 67.19% ሰራተኛ ተጠቃሚ አይደለም ማለት ይቻላል፤ አማካዩ

1.11 መሆኑም ይህን እዉነታ ያመለክታል፡፡

4.1.1.4. ለኢኮቴ የተሰጠዉ ትኩረት

ሠንጠረዥ 14 ለኢኮቴ የተሰጠው ትኩረት ለኢኮቴ የተሰጠ ትኩረት ምንም ዝቅተኛ መካከለኛ ከፍተኛ አማካይ

(Mean) ስታንዳርድ ዲቬዥን (SD)

ለኢኮቴ የሚመደብ የበጀት ድርሻ 27.04% 46.78% 21.89% 4.29% 2.03 .81 ኢኮቴን አስመልክቶ የተዘጋጀ አዉደጥናት፣ አጫጭር ስልጠና ወዘተ.. ብዛት

50.22% 33.33% 15.58% .87% 1.67 .77

ለኢኮቴ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ምቹ የስራ ቦታ

26.50% 32.05% 36.32% 5.13% 2.20 .89

ራሱን የቻለ የስልጠና ማዕከል መዘጋጀቱ

60.52% 21.03% 14.16% 4.29% 1.62 .88

ራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል መዘጋጀቱ 72.25% 19.82% 6.17% 1.76% 1.37 .68 የቪዲዮ ኮንፈረንስ አዳራሽ ራሱን ችሎ መኖሩና በተገቢዉ ሳቁስ መደራጀቱ

59.83% 19.66% 14.96% 5.56% 1.66 .93

በተቋሙ ዉስጥ ኢኮቴን አስመለክ በባለሙያዎች /በኃላፊዎች የተደረገ ጥናትና ምርምር ብዛት

80.00% 14.89% 4.68% .43% 1.26 .56

ራሱን የቻለ ሰርቨር ሩም መኖሩ 66.23% 11.84% 12.72% 9.21% 1.65 1.02 በኢኮቴ የሰለጠነ የሰዉ ኃይል ብዛት 19.74% 45.06% 31.76% 3.43% 2.19 .79

ከላይ በሰንጠረዥ 14 እንደተመለከተዉ ለኃላፊዎች ከተሰራጨ መጠይቅ በተገኘዉ ምላሽ

ለኢኮቴ ስለተሰጠ ትኩረት መረዳት እንደሚቻለዉ በጣም ትኩረት የተሰጠዉ በኢኮቴ

የሰለጠነ የሰዉ ኃይል (80.26%) ትልቁን ድርሻ ይይዛል፡፡ አማካይ መጠኑ 2.19 መሆኑ

የሚያመላክተዉ ግን በኢኮቴ የሰለጠ የሰዉ ኃይል ዝቅተኛ መሆኑን ነዉ፡፡ በመቀጠል

ለኢኮቴ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ምቹ የስራ ቦታ 73.50% ሲሆን፣ ከዚህ በመቀጠል ለኢኮቴ

የሚመደብ በጀት የራሱ ድርሻ እንዳለው የገለጹ መላሾች 72.96% ናቸው፤ በአጠቃላይ

ለኢኮቴ በተሰጠዉ ትኩረት ላይ የተነሱ ጉዳዮች ከሁለቱ በስተቀር በጀትን ጨምሮ

አማካያቸዉ ከ1.5-2.5 ስለሆነ ትኩረቱ ዝቅተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡ በተቃራኒዉ ለኢኮቴ

የተሰጠዉ ትኩረት በጣም ዝቅተኛ ሆኖ የሚታየዉ ኢኮቴን አስመልክቶ የተደረገ ጥናትና

Page 32: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

22

ምርምር 20% ሲሆን ራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል መኖሩ የሚለው 27.75% ነዉ፡፡ የእነዚህ

አማካይ ዉጤት 1.37 እና 1.26 በቅደም ተከተል መሆኑ ደግሞ ኢኮቴን አስመልክቶ

የተደረገ ጥናትና ምርምር እንዲሁም ራሱን የቻለ ስልጠና ማዕከል ለአብዛኛው ተቋማት

አለመኖሩን እንረዳለን፡፡ በአጠቃላይ ለኢኮቴ የተሰጠ ትኩረት በአማካይ ዝቅተኛ (1.73)

ነው፡፡

4.1.2. በኢኮቴ ባለሙያዎች ደረጃ ግምገማ

ለ296 ያህል የኢኮቴ ባለሙያዎች ከተሰራጨዉ መጠይቅ ዉስጥ በትክክል መጠይቁን

ሞልተዉ የመለሱት 200 ብቻ ናቸዉ፡፡ ከነዚህ መካከልም የኢኮቴ ባለሙያዎች እና

የኢኮቴ የስራ ሂደት አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል፤ በወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች አካባቢ

የኢኮቴ ባለሙያ ስለሌለ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የኢኮቴ መምህራን መጠይቁን

እንዲሞሉ ተደርጓል፡፡

4.1.2.1. የኢኮቴ ባለሙያዎች አጠቃላይ የግል ሁኔታ ከታች በሰንጠረዥ 15 እንደምንረዳዉ 75% ምላሹን የሰጡ የኢኮቴ ባለሙያዎች /የኢኮቴ

ስራ ሂደት አስተባባሪዎች/ መምህራን ወንድ ሲሆኑ ቀሪዎቹ 25% ሴቶች ናቸዉ፡፡

አብዛኛዉ ከ18-27 አመት የዕድሜ ክልል ዉስጥ ሲገኙ ጥናቱ በአብዛኛዉ በወረዳ ያሉ

ባለሙያዎችን (46%) ያቅፋል፡፡

Page 33: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

23

ሰንጠረዥ 15 የኢኮቴ ባለሙያዎች አጠቃላይ መረጃ አጠቃላይ መረጃ መቶኛ % ጾታ

ወንድ 75.00% ሴት 25.00%

ዕድሜ

18 — 27 ዓመት 60.91% 28 — 37 ዓመት 26.90% 38 — 47 ዓመት 10.15% ከ 47 ዓመት በላይ 2.03%

የስራ ቦታ

በክልል 10.77% ከተማ አስተዳደር 14.36% ዞን 28.21% ወረዳ 46.67%

የትምህርት ደረጃ

ሠርቲፊኬትና በታች 1.54% ዲፕሎማ 50.26% የመጀመሪያ ዲግሪ 44.62% ሁለተኛ ዲግሪና በላይ 3.59%

የአገልግሎት ዘመን

ከ5 ዓመት በታች 53.81% ከ5 - 10 ዓመት 28.93% ከ11 - 15 ዓመት 6.09% ከ15 ዓመት በላይ 11.17%

የኢኮቴ/ተዛማጅ ስልጠና ማስረጃ

የለኝም 21.28% ሠርቲፊኬት 25.53% ዲፕሎማ 39.36% ከዲፕሎማ በላይ 13.83%

የኢኮቴ ተደራሽነት

በጭራሽ 2.11% መንግስታዊ ተቋም 9.15% እንደ ኢንተርኔት ካፌ ያሉ ሌሎች ተቋማት 77.46% በመኖሪያ ቤት 11.27%

የተጠኝዎቹ የትምህርት ደረጃ ግማሽ በግማሽ (50%) ዲፕሎማ ነዉ፤ ከመላሾቹ መካከል

44.62% የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸዉ፡፡ የተጠኝዎችን የስራ ልምድ ስንመለከት 53.81%

የሚሆኑት ከ5 ዓመት በታች ያገለገሉ ናቸው፡፡ ከመላሾቹ መካከል ቀጥተኛ በኢኮቴ ወይም

ተዛማጅ በሆነ የትምህርት ዘርፍ 78.72% ያህሉ ሰልጥነዉ ማስረጃ አግኝተዋል፡፡

ከተጠኝዎቹ መካከል 97.89% የሚሆኑት የኢኮቴ አገልግሎት ያገኛሉ፤ ከነዚህ ዉስጥ

9.15% በመንግስት ተቋማት፣ 77.46 % (ከፍተኛዉ ድርሻ) እንደ ኢንተርኔት ካፌ ያሉ

መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት እንዲሁም 11.27% በመኖሪያ ቤታቸዉ አገልግሎቱን

ያገኛሉ፡፡

Page 34: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

24

4.1.2.2. የኢኮቴ ባለሙያዎች የኢኮቴ ዕዉቀት

ሰንጠረዥ 16 የኢኮቴ ባለሙያዎች የኢኮቴ ዕዉቀት የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን ምንም ዝቅተኛ መካከለኛ ከፍተኛ አማካይ

(Mean) ስታንዳርድ ዲቬዥን (SD)

የማክሮሶፍት ወርድ ዕዉቀት 1.02% 7.65% 21.43% 69.90% 3.60 .68 የማይክሮሶፍት ኤክሴል እዉቀት 2.04% 11.22% 27.55% 59.18% 3.44 .77 የማክሮሶፍት አክሰስ እዉቀት 6.19% 18.56% 37.11% 38.14% 3.07 .90 የፓወር ፖይንት እዉቀት 7.69% 10.26% 24.62% 57.44% 3.32 .94 የኢሜል መላላክ እዉቀት 9.84% 13.47% 18.13% 58.55% 3.25 1.03 የመረጃ መበርበሪያ (Search Engine) የመጠቀም እዉቀት

11.22% 14.29% 21.94% 52.55% 3.16 1.05

በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት የመጠቀም እዉቀት

9.79% 13.92% 20.10% 56.19% 3.23 1.02

የተለሙ ሶፍትዌር እዉቀት 15.10% 11.98% 29.17% 43.75% 3.02 1.08 አይፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ የመጠቀም እዉቀት

23.16% 21.05% 26.32% 29.47% 2.62 1.14

የLAN ዝርጋታ መሰረታዊ ዕዉቀት 15.82% 22.96% 28.06% 33.16% 2.79 1.07 የኔትወርክ አስተዳደር ዕዉቀት 18.56% 16.49% 39.18% 25.77% 2.72 1.05 ሶፍትዌርና ዳታ ቤዝ የማልማት እዉቀት 21.65% 31.44% 34.02% 12.89% 2.38 .97 ሃርድዌርና ሶፍትዌር ጥገና እዉቀት 17.44% 22.05% 42.05% 18.46% 2.62 .98 ድረ-ገጽ የማልማትና የማሻሻል እዉቀት 27.32% 21.44% 32.47% 8.76% 2.23 .95 አዳዲስ ኦፕሬቲንግ ሶፍትዌር እዉቀት 13.92% 15.46% 31.96% 38.66% 2.95 1.05 አድቫንስድ የኮምፒውተር ቋንቋ እዉቀት 29.23% 30.77% 33.33% 6.67% 2.17 .93 የትምህርት መርጃ ሲሙሌሽን የመጠቀም ዕዉቀት*

30.88% 33.82% 19.12% 16.18% 2.21 1.06

*በኢኮቴ መምህራን ብቻ በተጨማሪ የተሞላ

ከላይ በሰንጠረዥ 16 እንደተመለከተዉ የኢኮቴ ባለሙያዎች ካላቸዉ እዉቀት

የመጀመሪያዉን ስፍራ 98.98% የሚይዘዉ እንደ ማይክሮሶፍት ያሉ የወርድ ፕሮሰሲንግ

እዉቀት ሲሆን የዚህ እዉቀት አማካይ ደግሞ 2.6 መሆኑም የሚያመለክተዉ ባለሙያዎቹ

ያላቸዉ ዕዉቀት ከፍተኛ መሆኑን ነዉ፡፡ በመቀጠል በተከታታይ የማይክሮሶፍት ኤክሴል

ስፕሪድ ሽት፣ የማክሮሶፍት አክሰስ፣ ፓወርፖይንት፣ በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት

የመጠቀም፣ ኢሜል የመላላክ፣ የመረጃ መበርበሪያ መሳሪያ የመጠቀም፣ አዳዲስ ኦፕሬቲንግ

ሶፍትዌር፣ የተለሙ አፕሊኬሽን ሶፍትዌሮችን የመጠቀም፣ የLAN ዝርጋታ ዕውቀት፣

ሃርድዌርና ሶፍትዌር ጥገና፣ የኔትወርክ አስተዳደር እንዲሁም አይ.ፒ ሚሴንጀር፣

ኔትሚቲንግና ሚሴጅ ፖፕአፕ የመጠቀም እዉቀት በቅደም ተከተል 97.6% 93.81%፣

Page 35: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

25

92.31%፣ 90.21%፣ 90.16%፣ 88.78%፣ 86.08%፣ 94.90%፣ 84.18%፣ 82.56%፣ 81.44

እና 76.84% ሲሆን አማካያቸዉም ከ2.5 — 3.49 በመሆኑ ባለሙያዎቹ በእነዚህ ጉዳዮች

ዙሪያ መካከለኛ እዉቀት እንዳላቸዉ እንረዳለን፡፡ ሶፍትዌርና ዳታ ቤዝ የማልማት

ዕዉቀት 78.35% ቢሆንም አማካዩ 2.38 መሆኑ ባለሙያዎቹ ያላቸዉ ዕዉቀት ዝቅተኛ

ነዉ፡፡ በመጨረሻዎቹ ረድፍ ቤተሙከራን የሚተካ ሲሙሌሽን ዕዉቀት (69.12%)፣

የአድቫንስድ ኮምፒዩተር ቋንቋ ዕዉቀት (70.77%)፣ ድረ ገጽ የማልማት ዕዉቀት

(72.68%) ሲሆኑ የኢኮቴ ባለሙያ፣ አስተባባሪ ወይም መምህራን ዕዉቀት አማካይም

በቅደም ተከተል 2.21፣ 2.17፣ 2.23 መሆኑ የሚያሳየዉ ባለሙያዎቹ ያላቸዉ ዕዉቀት

ዝቅተኛ መሆኑን ነዉ፡፡

4.1.2.3. የባለሙያዎች የኢኮቴ አጠቃቀም

ሰንጠረዥ 17 የባለሙያዎች የኢኮቴ አጠቃቀም የኢኮቴ አገልግሎት አጠቃቀም በጭራሽ አልፎ

አልፎ በተደጋጋሚ ሁልጊዜ አማካይ

(Mean) ስታንዳርድ ዲቬዥን (SD)

የማክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም 2.12% 10.58% 24.87% 62.43% 3.48 .77 የማይክሮሶፍት ኤክሴል አጠቃቀም

6.95% 25.67% 25.67% 41.71% 3.02 .98

የማክሮሶፍት አክሰስ እዉቀት 16.49% 34.57% 27.13% 21.81% 2.54 1.01 የፓወር ፖይንት አጠቃቀም 14.52% 26.88% 27.42% 31.18% 2.75 1.05 የኢሜል መላላክ አጠቃቀም 22.04% 19.89% 28.49% 29.57% 2.66 1.12 የመረጃ መበርበሪያ መሳሪያ አጠቃቀም

21.39% 22.46% 24.60% 31.55% 2.66 1.14

በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት አጠቃቀም

16.13% 25.27% 24.73% 33.87% 2.76 1.09

የLAN ዝርጋታ አጠቃቀም 22.04% 26.34% 19.89% 31.72% 2.61 1.15 የተለሙ ሶፍትዌር አጠቃቀም 21.81% 27.66% 27.66% 22.87% 2.52 1.07 አይፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ አጠቃቀም

36.17% 29.79% 20.21% 13.83% 2.12 1.05

የትምህርት መርጃ ሲሙሌሽን አጠቃቀም*

32.31% 36.92% 23.08% 7.69% 2.06 .93

*በኢኮቴ መምህራን ብቻ በተጨማሪ የተሞላ

Page 36: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

26

ከላይ በሰንጠረዥ 17 እንደተመለከተዉ የኢኮቴ ባለሙያዎች፣ አስተባባሪዎች ወይም

መምህራን የማይክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም 97.88% በመሸፈን የመጀመሪያዉን ደረጃ

ይይዛል፤ የዚሁ አማካይም 3.48 መሆኑ ባለሙያዎች ማይክሮሶፍት ወርድን በተደጋጋሚ

እንደሚጠቀሙበት ይጠቁማል፡፡ በመቀጠል የማይክሮሶፍት ኤክሴል (93.05)፣ ፓወር

ፖይንት (85.48)፣ በሲዲ የተቀመጡ ኢ-መፃህፍትን /ኢንሳይክሎፒዲያ (83.87%)፣

ማይክሮሶፍት አክሰስ (83.51%)፣ እንደ ጉግል ያሉ የመረጃ መበርበሪያ (78.61%)፣

ኢሜል የመላላክና በላን ኔትወርክ መጠቀም (77.96%) ሲሆኑ ባለሙያዎቹ የሚጠቀሙበት

የአጠቃቀም ሁኔታም በተደጋጋሚ ነዉ፡፡ በዝቅተኛ ደረጃ አጠቃቀም የሚመደቡት አይ.ፒ

ሚሴንጀር፣ ሚሴጅ ፖፕ አፕ እና ኔት ሚቲንግ (63.83%) እንዲሁም ላቦራቶሪን የሚተካ

የትምህርት መርጃ ሲሙሌሽን (67.69%) አጠቃቀሞች ሲሆኑ የአጠቃቀም ሁኔታቸዉም

አልፎ አልፎ ነዉ፡፡

4.1.2.4. የኢኮቴ ተፅዕኖ

ሰንጠረዥ 18 የኢኮቴ ተፅዕኖ በኢኮቴ ባለሙያዎች እይታ የኢኮቴ ተፅዕኖ

(ሚን) Mean

ስታንዳርድ ዲቬዥን (SD)

በአጠቃላይ ኢኮቴ ስራዬን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድቶኛል 4.55 .84

ማይክሮሶፍት ወርድ ደብዳቤ፣ ዶክመንት ወዘተ ለማዘጋጀት ረድቶኛል 4.64 .80 ማይክሮሶፍት ኤክሴል ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ. ለማዘጋጀት ረድቶኛል 4.38 .97 ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ ረድቶኛል 3.97 1.35 የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን ጊዜንና ወጪን ቆጥቦልኛል 3.91 1.28 አይፒ ሚሴንጀር ኔት ሚቲንግ ወዘተ መጠቀም ሥራን ያቃልላል፣ ወጪንም ቆጥቧል

3.56 1.31

ወረዳኔት/ስኩልኔት የተለያየ አገልግሎቶች በየአካባቢዉ እንዲዳረሱ በማድረግ ገንዘብ ጊዜና ጉልበትን ቆጥቧል

3.68 1.24

ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል 4.20 1.14 ኢኮቴ የመስመር ላይ ድጋፍ ለማድረግ /ለመቀበል ረድቶኛል 3.75 1.20 ኢኮቴ የስራ ተነሳሽነቴን ጨምሮልኛል 4.25 1.01 ኢኮቴ አንዳንድ ማቴሪያሎችን በነፃ ለማግኘት አስችሎኛል 3.87 1.25 ኢኮቴ የአሠራር ዘዴን በማሻሻሉ ዉጣዉረድን አሳጥሯል 4.18 1.06 ኢኮቴ የሰራተኛዉን ብሎም የተቋሙን ስራ አፈፃፀም አሻሽሏል 4.03 1.05 ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ ልዉዉጥ በማከናወን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን ቆጥቧል

4.00 1.15

Page 37: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

27

ከላይ በሰንጠረዥ 18 እንደተመለከተዉ የማይክሮሶፍት ወርድ ደብዳቤ፣ ዶክመንት ወዘተ.

ለማዘጋጀት ይረዳል የሚለዉ በቀዳሚ ስፍራ አማካይ 4.64 በዝቅተኛ ስታንዳርድ ዲቬሽን

0.80 ላይ ይገኛል፤ በመሆኑም የማክሮሶፍት ወርድ አዎንታዊ ተፅዕኖው በጣም ጥሩ ደረጃ

ላይ መሆኑንና ሁሉም ባለሙያዎች ከአማካዩ በተቀራረበ ሁኔታ በሰጡት ምላሽ በአወንታዊ

ተጽዕኖው በጣም እንደሚስማሙ መረዳት ይቻላል፡፡ በተመሳሳይ በአጠቃላይ ኢኮቴ

ስራዬን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድቶኛል የሚለው ከፍተኛ አማካይ ዉጤት (4.55)

እንዲሁም ዝቅተኛ ስታንዳርድ ዲቬሽን (0.84) መሆኑ ኢኮቴ ስራን በፍጥነትና በጥራት

ለመስራት በጣም ጥሩ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደሚደርግ መረዳት ይቻላል፡፡ ከሰንጠረዡ

እንደምንረዳው ስለኢኮቴ ተፅዕኖ በተነሱ በሁሉም ጉዳዮች ላይ ከ2.5 በታች አማካይ

ዉጤት የለም፤ ይህ የሚያመለክተዉ መልስ ሰጭዎች ኢኮቴ በመንግስት አገልግሎት

አሰጣጣቸዉ ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተፅዕኖ አለማሳደሩን መስማማታቸዉን ነዉ፡፡

ማይክሮሶፍት ኤክሴል ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ. ለማዘጋጀት ረድቶኛል፣ኢንተርኔት መረጃን

በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ ረድቶኛል፣የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን ጊዜንና ወጪን

ቆጥቦልኛል፣አይፒ ሚሴንጀር ኔት ሚቲንግ ወዘተ መጠቀም ሥራን ያቃልላል፣ ወጪንም

ቆጥቧል፣ወረዳኔት/ስኩልኔት የተለያየ አገልግሎቶች በየአካባቢው እንዲዳረሱ በማድረግ

ገንዘብ ጊዜና ጉልበትን ቆጥቧል፣ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ

ረድቶኛል፣ኢኮቴ የመስመር ላይ ድጋፍ ለማድረግ /ለመቀበል ረድቶኛል፣ኢኮቴ የስራ

ተነሳሽነቴን ጨምሮልኛል፣ኢኮቴ አንዳንድ ማቴሪያሎችን በነፃ ለማግኘት

አስችሎኛል፣ኢኮቴ የአሠራር ዘዴን በማሻሻሉ ዉጣዉረድን አሳጥሯል፣ኢኮቴ የሰራተኛዉን

ብሎም የተቋሙን ስራ አፈፃፀም አሻሽሏል፣ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ

ልዉዉጥ በማከናወን ጊዜ፣ ጉልበትና ቦታንና ወጪን ቆጥቧል የሚሉት አማካያቸዉ ከ3.5 -

4.49 በመሆኑ በአገልግሎት አሰጣጣቸው ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደሚያደርጉ

ባለሙያዎቹ ይስማማሉ፡፡ ስለዚህ በተተነተኑት ሁሉም ጉዳዮች ላይ ኢኮቴ አወንታዊ

ተጽዕኖ አሳድሯል፡፡

Page 38: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

28

4.1.2.5 ኮሪሊሽን ከላይ ለተጠቀሱት የኢኮቴ ተፅዕኖዎች በተለይ በጣም ጥሩ የሆኑትን ለይተን ከተለያዩ

ቫሪያብልስ ጋር ያላቸዉን ኮሪሌሽን ማየት ጠቃሚ ነዉ፡፡

ሠንጠረዥ 19 የትምህርት ደረጃ፣ልምድና ስልጠና ኮሪሌሽን ኮሪሌሽን በአጠቃላይ የኢኮቴ ተፅዕኖ በአገልግሎት

አሰጣጥ ፍጥነትና ጥራት ላይ የማክሮሶፍት ወርድ ተፅዕኖ በአገልግሎት አሰጣጥ

የትምህርት ደረጃ .000 -.041 የስራ ልምድ .037 -.037 የኢኮቴ ስልጠና .193 .280 የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት

.362 .307

የኮርሌሽን ወሰን በ-1.00 እና 1.00 መካከል ነዉ፤ ዝምድናዉ ከ0 ወደ 1 በተጠጋ ቁጥር

የተሻለ ተዛማጅነት (ፖዚቲቭ ኮሪሌሽን) ሲኖራቸዉ በሌላ በኩል ዝምድናዉ ከ0 ወደ -1

ሲጠጋ የተቃርኖ ዝምድና (ኔጌቲቭ ኮርሌሽን) ይኖራቸዋል፡፡ ዜሮ ከሆነ ምንም አይነት

ኮሪሌሽን የላቸውም ማለት ነው፡፡ በዚህ መሰረት ከላይ በሰንጠረዥ 19 እንደምንረዳዉ

የኢኮቴ ስልጠናና የማክሮሶፍት ወርድ ተፅዕኖ የተሻለ አወንታዊ ዝምድና (0.280)

ሲኖራቸዉ ከዚያ ባነሰ የኢኮቴ ስልጠናና በአጠቃላይ የኢኮቴ ተፅዕኖ በአገልግሎት አሰጣጥ

ፍጥነትና ጥራት ላይ አወንታዊ ዝምድና (0.193) አላቸዉ፡፡ የስራ ልምድ ከአጠቃላይ

የኢኮቴ ተፅዕኖ በአገልግሎት አሰጣጥ ፍጥነትና ጥራት ላይ በጣም ዝቅተኛ አወንታዊ

ዝምድና (0.037) ሲኖረው ከማይክሮሶፍት ወርድ ተፅዕኖ ጋር በጣም ዝቅተኛ አሉታዊ

ዝምድና (-0.037) አለዉ፡፡ የትምህርት ደረጃ ከማይክሮሶፍት ወርድ ተፅዕኖ ጋር አሉታዊ

ዝምድና (-0.041) ሲኖረዉ ከአጠቃላይ የኢኮቴ ተፅዕኖ ጋር ምንም አይነት ዝምድና (0.0)

የለዉም፡፡ የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት ከአጠቃላይ የኢኮቴ ተፅዕኖ በአገልግሎት አሰጣጥ

ፍጥነትና ጥራት ላይ ከፍተኛ አወንታዊ ዝምድና (.362) ሲኖረው በተመሳሳይ

ከማይክሮሶፍት ወርድ ተፅዕኖ ጋር ከፍተኛ አወንታዊ ዝምድና (.307) አለው፡፡

በሌላ በኩል የኢኮቴ ዕዉቀትና አጠቃቀምን እና ተፅዕኖን ያላቸዉን ኮሪሌሽን

በማይክሮሶፍት ወርድ ተምሳሌት አድርገን ብንመለከት ከታች ከሰንጠረዥ 20

እንደምንመለከተዉ የማክሮሶፍት ዕዉቀትና አጠቃቀም ከፍተኛ ፖዚቲቭ ኮሪሌሽን (0.57)

Page 39: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

29

እንዲሁም የማይክሮሶፍት አጠቃቀም ከተፅዕኖ ጋር ከፍተኛ ፖዚቲቭ ኮሪሌሽን (0.40)

እንዳላቸዉ እንረዳለን፡፡

ሠንጠረዥ 20 የማይክሮሶፍት ወርድ ዕውቀት፣አጠቃቀምና ተጽዕኖ ኮሪሌሽን ኮሪሌሽን የማክሮሶፍት ወርድ

ዕዉቀት የማክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም

የማክሮሶፍት ወርድ ተፅዕኖ

የማክሮሶፍት ወርድ ዕዉቀት 1.00 0.57 0.47 የማክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም

0.57 1.00 0.40

የማክሮሶፍት ወርድ ተፅዕኖ 0.47 0.40 1.00

4.1.2.6. የኢኮቴ ባለሙያ /የሂደት አስተባባሪ/ መምህራን አስተያየት

ከታች በሰንጠረዥ 21 እንደምንመለከተዉ የኢኮቴ ባለሙያ /ሂደት አስተባባሪ/ መምህራን

የሁሉም ተቋማት መረጃ አያያዝና ልዉዉጥ በወረዳኔት፣ ስኩል ኔት እና በዌብቤዝድ ዳታ

ቤዝ መታገዝ አለባቸዉ ብለዉ ይስማማሉ፡፡ አማካዩ 4.70 መሆኑ የሚያሳየዉ የስምምነቱ

ደረጃ ከፍተኛ መሆኑን ነዉ፡፡ እነዚህ ባለሙያዎች በተመሳሳይ ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ

ተቋማት ኦቶሜት መደረግ አለባቸዉ (4.31) ብለዉ ይስማማሉ፡፡

ሰንጠረዥ 21 የኢኮቴ ባለሙያ /ሂደት አስተባባሪ/ አስተያየት የኢኮቴ ባለሙያ /ሂደት አስተባባሪ/ አስተያየት ሚን

(Mean) ስታንዳርድ ዲቪዥን (SD)

ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት አቶሜት መደረግ አለባቸዉ፡፡

4.31 1.04

የሁሉም ተቋማት መረጃ አያያዝና ልዉዉጥ በወረዳኔት፣ ስኩል ኔት እና በዌብቤዝድ ዳታ ቤዝ መታገዝ አለባቸዉ

4.70 3.04

4.1.3. በሰራተኛ ደረጃ ግምገማ

በአጠቃላይ ከተሰራጨው 456 መጠይቅ ውስጥ በትክክል መጠይቁን ሞልተዉ የመለሱ

ሠራተኞች 399 ሲሆኑ በሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶችን የሚወክሉ በክልል፣ ከተማ

አስተዳደር እና ዞን ሴክተሮች ሁለት ሁለት እንዲሁም በወረዳ የሚገኙ ጽ/ቤቶች ላይ

አንድ ሰራተኛ እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡

Page 40: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

30

4.1.3.1 አጠቃላይ የስራተኞች የግል ሁኔታ

ሠንጠረዥ 22 የሰራተኞች አጠቃላይ የግል ሁኔታ አጠቃላይ የግል ሁኔታ መቶኛ ፆታ• ወንድ 68.54%

ሴት 31.46% እድሜ

18-27 ዓመት 39.65% 28-37 ዓመት በክልል

35.86%

38-47 ዓመት 18.94% ከ47 ዓመት በላይ 5.56%

የስራ ቦታ

በክልል 13.16% ከተማ አስተዳደር 14.68% ዞን 42.78% ወረዳ 29.37%

የትምህርት ደረጃ

ሰርተፍኬትና በታች 2.53% ዲፕሎማ 31.57% የመጀመሪያ ዲግሪ 59.60% ሁለተኛ ዲግሪና በላይ

6.31%

የአገልግሎት ዘመን

ከ5 ዓመት በታች 31.47% ከ5-10 ዓመት 27.92% ከ11-15 ዓመት 14.97% ከ15 ዓመት በላይ 25.63%

የኢኮቴ/ተዛማጅ ስልጠና ማስረጃ

የለኝም 36.06% ሠርተፍኬት 44.76% ዲፕሎማ 16.37% ከዲፕሎማ በላይ 2.81%

የኢኮቴ ተደራሽነት

በጭራሽ 19.67% መንግስታዊ ተቋም 59.56% እንደ ኢንተርኔት ካፌ ያሉ ሌሎች ተቋማት

13.39%

በመኖሪያ ቤት 7.38%

Page 41: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

31

በሰንጠረዥ 22 እንደተመለከተዉ ከ399 ሰራተኞች ዉስጥ አብዛኛዉ (68.54%) ወንዶች

ሲሆኑ 31.46% ደግሞ ሴቶች ናቸዉ፡፡ ዕድሜያቸዉም በአብላጫዉ (39.65%) ከ18-27

ዓመት ክልል ዉስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡ ከ47 ዓመት በላይ የሆኑት 5.65% ብቻ ናቸዉ፡፡

ከተጠኝዎቹ መካከል በዞን 42.78% የሚሰሩ ሲሆን በወረዳ ደግሞ 29.37% ያህሉ

በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ የትምህርት ደረጃቸዉም አብዛኞቹ (59.60%) የመጀመሪያ ዲግሪ

ሲኖራቸዉ 31.57% ደግሞ ዲፕሎማ ናቸዉ፡፡ የሰራተኞቹ የአገልግሎት ዘመን ከ5 ዓመት

በታች 31.47% ሲሆን ከ15 ዓመት በላይ ያገለገሉ 25.63% ናቸው፡፡ 36.06% ምንም

አይነት የኢኮቴ ወይም ተዛማጅ ስልጠና ማስረጃ የሌላቸዉ ሲሆኑ ቀሪዎቹ 63.94%

የስልጠና ማስረጃ አላቸዉ፡፡ ከነዚህም ዉስጥ ከፍተኛው ቁጥር (44.76%) ሰርቲፊኬት

አላቸዉ፡፡ በአጠቃላይ 80.33% የሚሆኑት የኢኮቴ አገልግሎት ሲያገኙ 19.67% ምንም

አይነት የኢኮቴ አገልግሎት አያገኙም፡፡ አገልግሎት ከሚያገኙት ዉስጥ አብዛኛዉ

(59.56%) አገልግሎቱን ከመንግስት ተቋማት ያገኛሉ፡፡ 7.36% ደግሞ በመኖሪያ ቤታቸዉ

የኢኮቴ አገልግሎትን ያገኛሉ፡፡

4.1.3.2. የኢኮቴ እውቀት

ሠንጠረዥ 23 የሰራተኞች የኢኮቴ ዕውቀት

የኢኮቴ ዕውቀት

ምንም

ዝቅተኛ

መካከለኛ

ከፍተኛ

አማካኝ (Mean)

ስታንዳር ዲቪዥን (SD)

የማይክሮሶፍት ወርድ እውቀት 7.59% 21.77% 45.06% 25.57% 2.89 .88

የማይክሮሶፍት ኤክስል እውቀት 17.17% 33.84% 36.11% 12.88% 2.45 .92

የማይክሮሶፍት አክሰስ እውቀት 32.82% 39.79% 21.19% 6.20% 2.01 .89

የፓወር ፖይንት እውቀት 34.36% 25.90% 30.51% 9.23% 2.15 1.00

የኢሜል መላላክ እውቀት 36.71% 27.59% 22.78% 12.91% 2.12 1.05

የመረጃ መበርበሪያ መሳሪያ የመጠቀም

እውቀት

40.56% 24.74% 22.96% 11.73% 2.06 1.05

u CD/RAM የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት

የመጠቀም እውቀት

34.26% 27.46% 27.20% 11.08% 2.15 1.02

የተለሙ ሶፍትዌር እውቀት 46.86% 30.63% 18.06% 4.45% 1.80 .89

አይ.ፒ ሜሴንጀርና ኔትሚቲንግ የመጠቀም

እውቀት

62.34% 25.70% 9.92% 2.04% 1.52 .76

Page 42: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

32

መረጃዉ በተሰበሰበባቸዉ የመንግስት ተቋማት ከሚሰሩ ሠራተኞች ውሥጥ የማይክሮሶፍት

ወርድ እዉቀት ቀዳሚዉ (92.41%) ሲሆን አማካይ ዉጤቱም 2.89 ነው፡፡ ይህ

የሚያመለክተዉ የሰራተኞች የማክሮሶፍት ወርድ ዕዉቀት መካከለኛ መሆኑን ነዉ፡፡

በመቀጠል የማይክሮሶፍት ኤክሴል እውቀት (82.83%) ቢሆንም የሰራተኞቹ አማካይ 2.45

በመሆኑ የእዉቀት ደረጃዉ ዝቅተኛ ነዉ፡፡ በአጠቃላይ የማይክሮሶፍት አክሰስ፣

በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-መፃህፍትና ኢንሳይክሎፒዲያ የመጠቀም፣ የፓወር ፖይንት፣

ኢ-ሜይል የመላላክ እንደ ጎግል ያሉ የመረጃ መበርበሪያ /search engine/ የመጠቀም፣

የተለሙ ሶፍትዌሮችን የመጠቀም ዕዉቀት እና አይ.ፒ ሜሴንጀር/ ኔትሚቲንግ ወዘተ.

የመጠቀም ዕዉቀት 67.10%፣ 65.74%፣ 65.64%፣ 63.79%፣ 59.44%፣ 53.14% እና

37.66% በቅደም ተከተል ሲሆን የሁሉም አማካይ ከ1.5 እስከ 2.49 መሆኑ የሚያሳየን

የሰራተኞች ዕዉቀት ደረጃዉ ዝቅተኛ መሆኑን ነዉ፡፡ በተለይ የኢይ.ፒ ሚሴንጀር፣ ሚሴጅ

ፖፕ አፕ እና ኔትሚቲንግ ወዘተ. ዕዉቀት ከ50% በታች አማካዩም 1.52 ስለሆነ የእውቀት

ደረጃው በጣም ዝቅተኛ መሆኑን እንረዳለን፡

4.1.3.3 የኢኮቴ አጠቃቀም ሠንጠረዥ 24 የሰራተኞች የኢኮቴ አጠቃቀም

የኢኮቴ አጠቃቀም

በጭራሽ

አልፎ አልፎ

በተደጋጋሚ

ሁሉጊዜ

አማካይ(Mean)

ስታንዳርድ ዲቬሽን (SD)

የማይክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም 14.39% 26.26% 24.49% 34.85% 2.80 1.07

የማይክሮሶፍት ኤክሴል አጠቃቀም 28.86% 33.67% 20.00% 17.47% 2.26 1.06

የማይክሮሶፍት አክሰስ አጠቃቀም 55.50% 30.43% 9.97% 4.09% 1.63 .83

የፖወር ፖይንት አጠቃቀም 47.59% 32.41% 13.92% 6.08% 1.78 .90

የኢሜል- መላላክ አጠቃቀም 54.50% 23.65% 10.54% 11.31% 1.79 1.03

የመረጃ መበርበሪያ መሣሪያ አጠቃቀም

52.30% 24.74% 13.78% 9.18% 1.80 .99

በሲዲ/ራም የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት አጠቃቀም

42.35% 35.46% 15.05% 7.14% 1.87 .92

የLAN ዝርጋታ አጠቃቀም 60.97% 21.68% 9.18% 8.16% 1.65 .95

የተለሙ ሶፍትዌር አጠቃቀም 63.33% 22.31% 9.49% 4.87% 1.56 .85

የአይፒ ሜሴንጀር፤ ኔትሚትንግ አጠቃቀም

76.14% 16.75% 4.57% 2.54% 1.34 .68

Page 43: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

33

በሠንጠረዥ 24 እንደተመለከተዉ የሰራተኛዉ የማይክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም 85.61%

ቀዳሚ ሲሆን አማካዩ 2.80 መሆኑ የሚያሳየው ሠራተኛዉ ማይክሮሶፍት ወርድን

በተደጋጋሚ እንደሚጠቀም ነው፡፡ በመቀጠል የተሻለ አጠቃቀም ያለው የማይክሮሶፍት

ኤክሴል 71.14% ሲሆን የአጠቃቀም ሁኔታውም አልፎ አልፎ እንደሆነ ከአማካዩ (2.26)

እንረዳለን፡፡ በመቀጠል በሲዲ የተቀመጡ ኢ- መጽሐፍት/ ኢንሳይክሎፔዲያ አጠቃቀም

(57.65%)፣ የፓወር ፖይንት አጠቃቀም (52.41%) የተሻሉ ቢሆኑም የሰራተኛዉ

የአጠቃቀም ሁኔታ የሚያስረዳን ግን አልፎ አልፎ እንደሚጠቀማቸዉ ነዉ፡፡ ሌሎቹ

ከተሻለ ወደ ዝቅተኛ የአጠቃቀም ደረጃ በቅደም ተከተል እንደ ጉግል ያሉ የመረጃ

መበርበሪያ /search engine/ የመጠቀም፣ ኢ-ሜይል የመላላክ፣ የማክሮሶፍት አክሰስ፣

የLAN ዝርጋታ እና የተለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች የመጠቀም ሁኔታ ሲሆኑ ሁሉም

የሠራተኛዉ የአጠቃቀም ሁኔታ አልፎ አልፎ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ነገር ግን አይ.ፒ

ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ. አጠቃቀም በጣም አናሳ (23.86%) መሆኑን እንረዳለን፤

አማካዩም 1.34 መሆኑ አብዛኛው (76.14%) በጭራሽ እንደማይጠቀሙ እንረዳለን፡፡

4.1.3.4 የኢኮቴ ተፅዕኖ

ሠንጠረዥ 25 የኢኮቴ ተፅዕኖ በሰራተኞች አይታ

የኢኮቴ ተፅዕኖ

ሚን (Mean)

ስታንዳርድ ዲቪዥን (SD)

በአጠቃላይ ኢኮቴ ሥራዬን በፍጥነትና በጥራት ለመሥራት ረድቶኛል፣ 4.17 1.05 ማይክሮሶፍት ወርድ ደብዳቤ፣ ዶኩመንት ወዘተ.ለማዘጋጀት ተድቶኛል፣ 4.22 1.02 ማይክሮሶፍት ኤክሴል ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ.ለማዘጋጀት ረድቶኛል፣ 3.80 1.23 ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኝትና ለመለዋወጥ ረድቶኛል፣ 3.57 1.34 የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን ጊዜንና ወጨን ቆጥቦልኛል፣ 3.69 3.35 አይፒ ሜሴንጀር ኔት ሚቲንግ ወዘተ. መጠቀም ሥራን ያቃልላል፣ ወጨንም ቆጥቧል

3.17 1.26

ወረዳኔት/ስኩል ኔት የተለያዩ አገልግሎቶች በየአካባቢው እንዲዳረሱ በማድረግ ገንዘብ ፣ ጊዜና ጉልበትን ቆጥቧል፣

3.39 1.31

ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረደቶኛል፣ 3.80 1.19 ኢኮቴ የመስመር ላይ ድጋፍ ለማድረግ/ለመቀበል ረድቶኛል፣ 3.29 1.25 ኢኮቴ የሥራ ተነሳሽነቴን ጨምሮልኛል፣ 3.82 1.16 ኢኮቴ አንዳንድ ማቴርያሎችን በነፃ ለማግኘት አስችሎኛል፣ 3.49 1.32 ኢኮቴ የአሠራር ዘዴን በማሻሻሉ ውጣ ውረድን አሣጥሯል፣ 3.89 1.12 ኢኮቴ የሠራተኛውን ብሎም የተቋሙን ሥራ አፈፃፀም አሻሽሏል፣ 3.80 1.12 ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ ልውውጥ በማከናወን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን ቆጥቧል፣

3.91 2.94

Page 44: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

34

በመንግስት አገልግሎት አሠጣጥ ላይ የኢኮቴ ተፅዕኖ ምን እንደሚመስል ከሰንጠረዥ 25

እንደምናየዉ በአጠቃላይ ኢኮቴ ስራዬን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድቶኛል የሚለዉ

ቀዳሚ ሲሆን አማካዩ 4.17 መሆኑ የሚያሳየን አብዛኛዉ ሰራተኛ ኢኮቴ ስራን በፍጥነትና

በጥራት ለመስራት እንደሚያስችል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ተጽዕኖ እንዳደረገ

የሚስማማ መሆኑን ነዉ፡፡ በመቀጠል ማክሮሶፍት ወርድ ደብዳቤ፣ ዶክመንት ወዘተ.

ለማዘጋጀት ረድቶኛል የሚለዉ ሲሆን አማካዩ 4.22 መሆኑ የማይክሮሶፍት ወርድ

በሠራተኛዉ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዳለዉ ያመለክታል፡፡

በአጠቃላይ በአማካይ ዉጤት ከትልቁ ወደ ትንሹ ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ

ልዉዉጥ በማከናወን ጊዜ ጉልበትና ወጪን ቆጥቧል (3.91)፣ ኢኮቴ የአሰራር ዘዴን

በማሻሻሉ ዉጣ ዉረድን አሳጥሯል (3.89)፣ ኢኮቴ የስራ ተነሳሽነትን ጨምሯል (3.82)፣

ኢኮቴ የሰራተኛዉን ብሎም የተቋሙን ስራ አፈፃፀም አሻሽሏል (3.80)፡፡ ማክሮሶፍት

ኤክሴል ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ. ለማዘጋጀት ረድቶኛል (3.80)፣ ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ

በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል (3.80)፣ የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን ጊዜንና

ወጪን ቆጥቧል (3.69)፣ እንዲሁም ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ

ረድቶኛል (3.57) የሚሉት ሲሆኑ ሠራተኛዉም በነዚህ በተነሱት የኢኮቴ ተፅዕኖዎች ላይ

ይስማማሉ፡፡ ነገር ግን ኢኮቴ አንዳንድ ቁሳቁሶችን /ማቴሪያሎችን በነፃ ለማግኘት

አስችሎኛል (3.49)፣ ወረዳኔት/ስኩልኔት የተለያዩ አገልግሎቶችን በየአካባቢዉ እንዲዳረሱ

በማድረግ ገንዘብ፣ ጊዜና ጉልበትን ቆጥቧል (3.39)፣ ኢኮቴ የመስመር ላይ ድጋፍ

ለማድረግ/ለመቀበል ረድቶኛል (3.29)፣ አይ.ፒ ሚሴንጀር/ኔትሚቲንግ ወዘተ. መጠቀም

ሥራን ያቃልላል፤ ወጪንም ቆጥቧል (3.17) የሚሉት ምንም አይነት ተፅዕኖ አላሳደሩም፡፡

በአጠቃላይ ግን ከተነሱት ሁሉም የኢኮቴ ተፅዕኖ ጉዳዮች ላይ በሰራተኛዉ የአገልግሎት

አሰጣጥ ላይ ኢኮቴ አሉታዊ ተፅዕኖ አለማሳደሩን እንገነዘባለን፡፡

Page 45: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

35

4.1.3.5 የሠራተኞች አስተያየት

ሠንጠረዥ 26 የሠራተኛው አስተያየት

የሰራተኛው አስተያየት አማካይ (Mean)

ስታንዳርድ ዲቬሽን (SD)

ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት ኦቶሜት መደረግ አለባቸው 4.21 1.04

የሁሉም ተቋማት መረጃ አያያዝና ሪፖርት ልውውጥ በወዳኔት፣ ስኩል ኔት፣

በዌብቤዝድ ዳታ ቤዝ መታገዝ አለባቸው

4.37 1.00

በሰንጠረዥ 26 እንደተመለከተዉ በቀዳሚነት የሁሉም ተቋማት መረጃ አያያዝና ሪፖርት

ልዉዉጥ በወረዳኔት፣ በስኩልኔት፣ በዌብ ቤዝድ ዳታ ቤዝ ወዘተ. መታገዝ አለባቸዉ፤

አማካዩ 4.37 መሆኑ የሚያሳየን ሠራተኛዉ በጉዳዩ እንደሚስማማ ነው፡፡ በመቀጠል

ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት ኦትሜት መደረግ አለባቸዉ (4.21)፤ እንደዚሁ

አብዛኛዉ ሠራተኛ እንደሚስማማ እንገነዘባለን፡፡

4.1.4 በበላይ ሃላፊ ደረጃ ግምገማ

ከተሰራጨዉ 296 መጠይቅ ዉስጥ 245 የበላይ ኃላፊዎች መጠይቁን በትክክል ሞልተዉ

የመለሱ ሲሆኑ ከሁሉም ተቋማት አንድ አንድ የበላይ ኃላፊ ወይም ተወካዮቻቸዉ

እንዲሞሉ ተደርጓል፡፡

Page 46: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

36

4.1.4.1 አጠቃላይ የበላይ ኃላፊዎች የግል ሁኔታ

ሠንጠረዥ 27 የበላይ ኃላፊዎች አጠቃላይ የግል ሁኔታ አጠቃላይ የግል ሁኔታ

መቶኛ

ጾታ ወንድ 84.55% ሴት 15.45%

ዕድሜ

18-27 13.06% 28-37 40.82% 38-47 35.92% ከ47 በላይ 10.20%

የሥራ ቦታ

ክልል 9.58% ከተማ አስተዳደር 15.42% ዞን 31.67% ወረዳ 43.33%

የትምህርት ደረጃ ሠርተፊኬትና በታች 1.23% ዲፕሎማ 22.63% የመጀመሪያ ድግሪ 64.61% ሁለተኛ ዲግሪና በላይ 11.52%

የአገልግሎት ዘመን ከ5 ዓመት በታች 12.24% ከ5-10 ዓመት 22.45% ከ11-15 ዓመት 21.22% ከ15 ዓመት በላይ 44.08%

የኢኮቴ/ተዛማጅ ሥልጠና ማስረጃ

የለኝም 40.66% ሠርተፊኬት 48.55% ዲፕሎማ 5.81% ከዲፕሎማ በላይ 4.98%

የኢኮቴ ተደራሽነት

በጭራሽ 20.00% መንግስታዊ ተቋም 62.79% እንደ ኢንተርኔት ካፌ ያሉ ሌሎች ተቋማት 8.84% በመኖሪያ ቤት 8.37%

በሰንጠረዥ 27 እንደምንመለከተዉ መጠይቁን ሞልተዉ ከመለሱት ዉስጥ 84.55%

ወንዶች 15.45% ሴቶች ናቸዉ፡፡ የዕድሜ ክልላቸዉ ደግሞ አብዛኞቹ (40.87%) ከ28 —

37 ዓመት ሲሆን ከ47 ዓመት በላይ ዕድሜ ያላቸዉ 10.20% ብቻ ናቸዉ፡፡ የስራ

ቦታቸዉም በአብዛኛዉ (43.33%) በወረዳ ሲሆን ዝቅተኛዉ (9.58%) በክልል ተቋማት

በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ አብዛኞቹ (64.61%) የበላይ ኃላፊዎች የትምህርት ደረጃቸው

የመጀመሪያ ዲግሪ ሲሆን 22.63% ደግሞ ዲፕሎማ አላቸዉ፡፡ የአገልግሎት ዘመናቸዉ

ደግሞ በአብዛኛዉ (44.08%) ከ15 ዓመት በላይ ሲሆን ዝቅተኛዉ (12.24%) ከ5 ዓመት

በታች ነዉ፡፡ በአጠቃላይ የኢኮቴ/ተዛማጅ ስልጠና ማስረጃ ያላቸዉ 59.34% ሲሆኑ ቀሪዉ

44.08% ምንም አይነት ማስረጃ የላቸዉም፡፡ 80% የሚሆኑት የኢኮቴ አገልግሎት ሲያገኙ

Page 47: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

37

ከዚህ ዉስጥ አብዛኞቹ (62.79%) በመንግስት ተቋማት አገልግሎቱን ያገኛሉ፡፡ 8.37%

የሚሆኑት መኖሪያ ቤታቸዉ የኢኮቴ አገልግሎት ያገኛሉ፡፡

4.1.4.2 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ ዕውቀት

ሰንጠረዥ 28 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ ዕውቀት

የኢኮቴ ዕውቀት

ምንም

ዝቅተኛ

መካከለ

ከፍተኛ አማካይ (mean)

ስታንዳርድ

ዲቬሽን

ማይክሮሶፍት ወርድ ዕውቀት፣ 14.88% 31.40% 38.02% 15.70% 2.55 .93

ማይክሮሶፍት ኤክሴል ዕውቀት፣ 26.14% 38.17% 27.39% 8.30% 2.18 .92

ማይክሮሶፍት አክሰስ ዕውቀት፣ 37.50% 42.92% 15.83% 3.75% 1.86 .82

የፖወር ፖይንት ዕውቀት፣ 32.78% 34.02% 24.07% 9.13% 2.10 .96

የኢሜል መላላክ ዕውቀት፣ 31.95% 31.54% 24.48% 12.03% 2.17 1.01

የመረጃ መበርበሪያ /search engine/

ዕውቀት፣

35.12% 31.82% 21.07% 11.98% 2.10 1.02

በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት

የመጠቀም ዕውቀት

34.98% 31.28% 23.05% 10.70% 2.09 1.00

የተለሙ ሶፍት ዌር ዕውቀት 46.69% 35.12% 14.46% 3.72% 1.75 .84

አይ ፒ ሜሴንጀር ፣ ኔት ሚቲንግ

የመጠቀም ዕውቀት ፣

61.41% 29.05% 5.81% 3.73% 1.52 .77

ከሰንጠረዥ 28 እንደምንረዳዉ የበላይ ኃላፊዎች የማክሮሶፍት ዕዉቀት የመጀመሪያዉን

(85.12%) ደረጃ ሲይዝ አማካዩ 2.55 መሆኑ የሚያሳየው የዕዉቀት መጠኑ መካከለኛ

እንደሆነ ነዉ፡፡ ሌሎቹ የኢኮቴ ዕዉቀት ከተሻለ ወደ ዝቅተኛ የማይክሮሶፍት ኤክሴል

(73.86%)፣ የኢ-ሜይል መላላክ (68.05)%፣ የፓወር ፖይንት (67.22%)፣ በCD/RAM

የተቀመጡ ኢ-መፃህፍትን የመጠቀም (65.02%) እንደ ጉግል ያሉ የመረጃ መበርበሪያ

/search engine/ የመጠቀም ዕዉቀት (64.88%) የማይክሮሶፍት አክሰስ (62.5%) ሲሆኑ

አማካያቸዉ ከ1.5 — 2.49 መሆኑ የሚያሳየዉ የኃላፊዎች ዕዉቀት ዝቅተኛ መሆኑን ነዉ፡፡

በተለይ የአይ.ፒ ሚሴንጀር፣ ኔት ሚቲንግ ወዘተ. ላይ ያለው የዕዉቀት ደረጃ በጣም

ዝቅተኛ (38.59%) መሆኑን እንገነዘባለን፡፡

Page 48: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

38

4.1.4.3 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ አጠቃቀም

ሠንጠረዥ 29 የበላይ ኃላፊዎች የኢኮቴ አጠቃቀም

ከሰንጠረዥ 29 እንደምንመለከተዉ የበላይ ኃላፊዎች ማይክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም

የመጀመሪያዉን ደረጃ (81.4%) ሲይዝ አማካዩ 2.96 መሆኑም የሚያሳይን የአጠቃቀም

ሁኔታዉ አንዳንድ ጊዜ መሆኑን ነዉ፡፡ ሌሎች በቅደም ተከተል የማይክሮሶፍት ኤክሴል

(67.63%)፣ በሲዲ/ራም የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት (64.58%)፣ የፓወር ፖይንት (62.66%)፣

የኢ-ሜይል መላላክ (58.26%)፣ እንደ ጉግል ያሉ የመረጃ መበርበሪያ /search engine/

(57.85%)፣ የማይክሮሶፍት አክሰስ (48.75%)፣ የLAN ዝርጋታ አጠቃቀም (39.33%)፣

የተለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች (38.98%) መሆኑ ሃላፊዎቹ ሁሉንም የሚጠቀሙት

አልፎ አልፎ መሆኑን ያመለክታል፡፡ አይ.ፒ ሜሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ. አጠቃቀም

(24.9%) ሲሆን አማካዩ 1.44 መሆኑ የበላይ ኃላፊዎች የአይ.ፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ

የኢኮቴ አጠቃቀም በጭራሽ አልፎ

አልፎ አንዳንድ

ጊዜ በተደጋጋ

ሚ በጣም

በተደጋጋሚ

አማካይ (Mean)

ስታንዳርድ

ዲቬሽን የማይክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም

18.60% 23.97% 18.18% 21.07% 18.18% 2.96 1.39

የማይክሮሶፍት ኤክሴል አጠቃቀም

32.37% 28.63% 19.50% 9.96% 9.54% 2.36 1.29

የማይክሮ ሶፍት አክሰስ አጠቃቀም

51.25% 25.83% 15.00% 5.00% 2.92% 1.83 1.05

የፓወር ፖይንት አጠቃቀም 37.34% 25.73% 20.33% 11.20% 5.39% 2.22 1.21 የኢሜል መላላክ አጠቃቀም 41.74% 25.21% 16.12% 8.68% 8.26% 2.17 1.28 የመረጃ መበርበሪያ መሳሪያ አጠቃቀም

42.15% 25.62% 13.64% 11.16% 7.44% 2.16 1.29

በሲዲ/ራም የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት አጠቃቀም

35.42% 30.83% 18.33% 9.17% 6.25% 2.20 1.20

የLAN ዝርጋታ አጠቃቀም 60.67% 15.06% 8.37% 8.37% 7.53% 1.87 1.30 የተለሙ ሶፍትዌሮች አጠቃቀም

61.02% 18.22% 11.02% 5.51% 4.24% 1.74 1.12

አይፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ አጠቃቀም

75.10% 13.28% 6.22% 3.32% 2.07% 1.44 .91

Page 49: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

39

ወዘተ. አጠቃቀም በጣም ዝቅተኛ መሆኑን እንረዳለን፤ 75.10% የሚሆኑት የአይ.ፒ

ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ. በጭራሽ አይጠቀሙም፡፡

4.1.4.4 የኢኮቴ ተፅዕኖ በበላይ ኃላፊዎች እይታ

ሠንጠረዥ 30 የኢኮቴ ተፅዕኖ በበላይ ኃላፊዎች እይታ

የኢኮቴ ተፅዕኖ አማካይ (Mean)

ስታንዳርድ ዲቬሽን

በአጠቃላይ ኢኮቴ ስራዬን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድቶኛል 4.21 .90 ማይክሮሶፍት ወርድ ደብዳቤ፣ ዶክመንት ወዘተ… ለማዘጋጀት ረድቶኛል

4.16 .94

ማክሮሶፍት ኤክሴል ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ.. ለማዘጋጀት ረድቶኛል 3.87 1.08 ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማገኘትና ለመለዋወጥ ረድቶኛል 3.53 1.28 የላን ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን ጊዜንና ወጪን ቆጥቦልኛል 3.48 1.21 አይፒ ሚሴንጀር ኔት ሚቲንግ ወዘተ መጠቀም ስራን ያቃልላል፣ ወጪንም ቆጥቧል

3.12 1.11

ወረዳኔት/ስኩል ኔት የተለያየ አገልግሎቶች በየአካባቢዉ እንዲዳረሱ በማድረግ ገንዘብ ጊዜና ጉልበትን ቆጥቧል

3.42 1.18

ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል 3.75 1.10 ኢኮቴ መስመር ላይ ድጋፍ ለማድረግ/ለመቀበል ረድቶኛል 3.34 1.05 ኢኮቴ የስራ ተነሳሽነቴን ጨምሮልኛል 3.80 1.01 ኢኮቴ አንዳንድ ማቴሪያሎችን በነፃ ለማግኘት አስችሎኛል 3.73 2.22 ኢኮቴ የአሰራር ዘዴን በማሻሻሉ ዉጣዉረድን አሳጥሯል 3.92 1.09 ኢኮቴ የሰራተኛዉን ብሎም የተቋሙን ስራ አፈፃፀም አሻሽሏል 3.80 1.07 ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ ልዉዉጥ በማከናወን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን ቆጥቧል

3.65 1.13

በሰንጠረዥ 30 እንደሚታየዉ በአጠቃላይ ኢኮቴ ስራዬን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት

ረድቶኛል የሚለው ቀዳሚዉ ሲሆን አማካዩ 4.21 መሆኑ ኢኮቴ በአገልግሎት አሰጣጥ

ፍጥነትና ጥራት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዳለዉ ኃላፊዎች እንደሚስማሙ እንረዳለን፡፡

በመቀጠልም የማክሮሶፍት ወርድ (አማካይ 4.16)፣ ኢኮቴ የአሰራር ዘዴን በማሻሻል ዉጣ

ዉረድን አሳጥሯል (አማካይ 3.90)፣ ማክሮሶፍት ኤክሴል ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ. ለማዘጋጀት

ረድቶኛል (አማካይ 3.87)፣ ኢኮቴ የስራ ተነሳሽነትን ጨምሯል እና ኢኮቴ የሰራተኛዉን

ብሎም የተቋሙን ስራ አፈፃፀም አሻሽሏል (አማካይ 3.8)፣ ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ

Page 50: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

40

በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል (አማካይ 3.75)፣ ኢኮቴ አንዳንድ ማቴሪሎችን

/ቁሳቁሶችን በነፃ ለማግኘት አስችሎኛል (አማካይ 3.73)፣ ኢኮቴን በመጠቀም ወረቀት

አልባ የመረጃ ልዉዉጥ በማከናወን ጊዜ፣ ጉልበት፣ ቦታና ወጪ ቆጥቧል (አማካይ 3.65)

እንዲሁም ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ ረድቶኛል (አማካይ 3.53)

የሚሉት አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዳላቸዉ አብዛኛዉ ኃላፊዎች እንደሚስማሙ ስንረዳ በሌላ

በኩል የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን ጊዜንና ወጪን ቆጥቧል (አማካይ 3.48)፣ ወረዳኔት/

ስኩል ኔት የተለያዩ አገልግሎቶችን በየአካባቢዉ እንዲዳረሱ በማድረግ ገንዘብ ጊዜና

ጉልበት ቆጥቧል (አማካይ 3.42 )፣ ኢኮቴ የመስመር ላይ ድጋፍ ለማድረግ /ለማግኘት

አስችሏል (አማካይ 3.34)፣ አይ.ፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ. መጠቀም ሥራን

ያቀላል፤ ወጪንም ይቆጥባል (አማካ 3.12) መሆኑ በኃላፊዎች አሰራር በሌላ አነጋገር

አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ምንም አይነት ተፅዕኖ እንዳልነበራቸዉ ወይም ስለጉዳዩ

እንደማያዉቁ መስማማታቸዉን እንገነዘባለን፡፡

4.1.4.5. የበላይ ኃላፊዎች አስተያየት

ሠንጠረዥ 31 የበላይ ኃላፊዎች አስተያየት

የኃላፊዎች አስተያየት አማካይ (Mean)

ስታንዳርድ ዲቬሽን

ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት ኦቶሜት መደረግ አለባቸዉ፡ 4.14 1.11 የሁሉም ተቋማት መረጃ አያያዝና ሪፖርት ልዉዉጥ በወረዳኔት፣ ስኩል ኔት፣ በዌብ ቤዝድ ዳታ ቤዝ መታገዝ አለባቸዉ

4.29 1.03

በሰንጠረዥ 31 እንደተመለከተዉ የሁሉም ተቋማት መረጃ አያያዝና ሪፖርት ልዉዉጥ

በወረዳኔት፣ ስኩልኔት፣ ዌብ ቤዝድ ዳታ ቤዝ መታገዝ አለባቸዉ የሚሉ አስተያየቶች

(አማካይ 4.29) እንዲሁም ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት ኦቶሜት መደረግ አለባቸዉ

(አማካይ 4.14) መሆኑ ሁሉም ኃላፊዎች በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ በከፍተኛ ደረጃ

እንደሚስማሙ እንረዳለን፡፡

4.1. 5. በደንበኞች ደረጃ ግምገማ ከተሰራጨው 296 መተየቅ ውስጥ 246 ደንበኞች መጠይቁን በትክክል ሞልተው የመለሱ

ሲሆን በክልል ቢሮዎች፣ ለከተማና ዞን መስተዳድሮች ሁለት በወረዳ ጽ/ቤቶች አንድ

ደንበኛ በጥናቱ እንዲካተቱ ተደርገዋል፡፡

Page 51: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

41

4.1.5.1 አጠቃላይ የግል ሁኔታ

ሠንጠረዥ 32 የደንበኞች አጠቃላይ የግል ሁኔታ አጠቃላይ የግል ሁኔታ መቶኛ ጾታ ወንድ 77.45%

ሴት 22.55% ዕድሜ 18-27 43.67%

28-37 35.92% 38-47 14.69% ከ47 በላይ 5.71%

የመኖሪያ ቦታ በክልል 6.94% ከተማ አስተዳደር 28.16% ዞን 20.41% ወረዳ 44.49%

የትምህርት ደረጃ ሰርቲፊኬትና በታች 14.29% ዲፕሎማ 37.14% የመጀመሪያ ዲግሪ 44.49% ሁለተኛ ዲግሪና በላይ 4.08%

የኢኮቴ/ተዛማጅ ስልጠና ማስረጃ

የለኝም 46.50% ሰርቲፊኬት 36.21% ዲፕሎማ 14.81% ከዲፕሎማ በላይ 2.47%

በሰንጠረዥ 32 እንደምንመለከተዉ መጠይቁን ከሞሉት 246 የተቋማት ደንበኞች ዉስጥ

77.45% ወንዶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 22.55% ሴቶች ናቸው፡፡ አብዛኛው 43.67% ከ18 — 27

ዓመት የዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ናቸዉ፡፡ የመኖሪያ ቦታቸዉም በአብላጫዉ

(44.49%) በወረዳ ነዉ፡፡ የትምህርት ደረጃቸዉ 44.49% የሚሆኑት የመጀመሪያ ዲግሪ

ያላቸዉ ሲሆን 37.14% የዲፕሎማ ምሩቃን ናቸዉ፡፡ በኢኮቴ/ተዛማጅ ስልጠና ማስረጃ

ያላቸው 53.50% ሲሆኑ ከእነዚህ ዉስጥ አብዛኛዉ ደንበኛ (36.21%) ሠርቲፊኬት

አላቸዉ፡፡

Page 52: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

42

4.1.5.2 የኢኮቴ ተፅዕኖ

•ሠንጠረዥ 33 የኢኮቴ ተፅዕኖ በደንበኞች እይታ

የኢኮቴ ተፅዕኖ

አማካይ (Mean)

ስታንዳርድ ዲቬሽን (SD)

የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመታገዙ ቀልጣፋና ውጤታማ ሆኗል፤

3.71 1.13

የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመታገዙ አገልግሎት አሰጣጡ አርክቶኛል፣

3.59 1.15

በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የታገዘ አገልግሎት በአካባቢዬ በማግኘቴ ጊዜ፣ጉልበትንና ወጪን ቆጥቦልኛል፤

3.73 1.17

የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመታገዙ አገልግሎት አሰጣጡ ግልጽና ፍትሃዊ ሆኗል፤

3.50 1.12

በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ምክንያት የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት ጨምሯል፤

3.45 1.18

በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ምክንያት የመስሪያ ቤቱ መረጃ አያያዝና አደረጃጀት ተሻሽሏል፤

3.65 1.20

በሰንጠረዥ 33 እንደተመለከተዉ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የታገዘ

አገልግሎት በአካባቢዬ በማግኘቴ ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ ቆጥቦልኛል የሚለዉ ቀዳሚ ሲሆን

አማካዩ 3.73 መሆኑ የሚያመለክተው ኢኮቴ ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ በመቆጠብ አዎንታዊ

ተፅዕኖ እንዳለዉ አብዛኛዉ ደንበኛ መስማማቱን ነዉ፡፡

በመቀጠል የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢኮቴ በመታገዙ ቀልጣፋና ዉጤታማ ሆኗል (አማካይ

3.71)፣ በኢኮቴ ምክንያት የመ/ቤቱ መረጃ አያያዝ ተሻሽሏል (አማካይ 3.65)፣ የመ/ቤቱ

አገልግሎት በኢኮቴ በመታገዙ አገልግሎት አሰጣጡ አርክቶኛል (3.59) እንዲሁም

የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢኮቴ በመታገዙ አገልግሎት አሰጣጡ ግልጽና ፍትሃዊ ሆኗል

(አማካይ 3.50) የሚሉት አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዳላቸዉ አብዛኛዉ ደንበኞች

መስማማታቸዉን እንረዳለን፡፡ በሌላ በኩል በኢኮቴ ምክንያት የመ/ቤቱ ሠራተኞች የሥራ

ተነሳሽነት ጨምሯል (አማካይ 3.45) መሆኑ በሠራተኛዉ ተነሳሽነት ላይ ኢኮቴ ምንም

አይነት ተፅዕኖ አለማሳደሩን ወይም ስለጉዳዩ ደንበኞች እንደማያዉቁ እንረዳለን፡፡

በተነሱት ሁሉም ጉዳዮች ላይ ኢኮቴ ምንም አይነት አሉታዊ ተፅዕኖ አለማሳደሩን

እንገነዘባለን፡፡

Page 53: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

43

4.2. የጥናቱ ውጤት ማብራሪያ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴከኖሎጅ በመንግስት አገልግሎት አሠጣጥ ላይ ያሳደረውን

ተፅዕኖ ለመዳሰስ በሚደረጉ ጥናቶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከዚህ ተፅዕኖ ጋር

ተዛማጅነት ያላቸውን ጉዳዮች ማየት ጠቃሚ ይሆናል፡፡ ሮቢን (ጁላይ 2011) እንዳለው

አዳዲስ ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ፣ ማስፋፋትና በህብረተሰቡ ውስጥ እንዲሰርፅ ማድረግ

እንዲህ በቀላሉ የሚቻል (Straight forward) አይደለም፤ የራሱ የሆነ መስናክሎች አሉት፤

ቢሆንም ባለፉት ዓመታት በርካታ አገራት ኢኮቴን በመጠቀማቸው በህብረተሰቡ ዘንድ

ቴክኖሎጂው ተፈላጊና ተቀባይነት እንዲያገኝ ሆኗል፡፡ የአገልግሎት አሠጣጡንም ጥራት፣

ቅልጥፍና ውጤታማነትና ብቃት በማሻሻሉ “ ብርማው ጥይት” (Silver Bullet) እስከ

መባል ደርሷል ፡፡ እንደሮቢን ገለፃ ኢኮቴን ለአገልግሎት አሰጣጥ ስኬት የሚያበረክተውን

ድርሻ በሶስት ደረጃ ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ እነርሱም

1. ዝግጁነት ( Readiness )

2. አጠቃቀም ( Use )

3. ተፅዕኖ (Impact ) ናቸው፡፡

ዝግጁነት የአጠቃቀም ቅድመ ሁኔታዎችን ያካትታል ፡፡ ለምሳሌ የኢኮቴ ተደራሽነትን

/ቴክኖሎጂውን በቀላሉ ማግኘትን/፣ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ወዘተ. ሲያካትት ተፅዕኖ

ደግሞ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚያስከትለውን ውጤት ይመለከታል ፡፡ ለምሳሌ

ወጪ፣ ጊዜና ጉልበት ከመቆጠብ ጋር ተያይዞ የመንግስትና ህብረተሰቡን ግንኙነት

ከማሻሻል አኳያ ሊታይ ይችላል፡፡ በአጠቃላይ የእነዚህን ትስስር ከታች በስዕል 1

እንደተቀመጠው ለማብራራት ይሞክራል ፡፡

Page 54: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

44

አጠቃላይ ዝግጁነት (General Readiness)

ቴሌኮም መሠረተ ልማት ( Telecom

Infrastructure )

የኢኮቴ ልማት ( ICT Skills )

ህብረተሰቡ ለቴክኖሎጂው ያለው አመኔታ

ምስጥርን ከመጠበቅና ከደህነት አንፃር

(Trust, Privacy & Security)

ኢ-መንግስት (E-government)

የመስመር ላይ አገልግሎት

(On line service provision)

የኢ.ኮ.ቴ.ል ስትራቴጂና ፖሊሲ

(Overall ICT Strategy and Policy)

አጠቃላይ አጠቃቀም (General use)

የኢኮቴ አጠቃቀም (Frequency of ICT

use)

ኢ-መንግስት አጠቃቀም (e-Government

use)

ኮሜርሽያል አጠቃቀም (e-Commerce)

ማህበራዊና ባህላዊ (social & cultural use)

መረጃ ለማግኘት ( Information Search )

ለመገናኛ (Communication)

ስዕል 1 የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ አጠቃላይ ፍሬም ወርክ

ጥራት (Quality)

አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል (Public

Service Improvement)

ውጤታማነት (Efficiency)

የመንግስት ወጭ መቀነስ

(Reduction of Government

Spending)

የህዝብ አመለካከት (Public

Openion) )

ህዝቡ ለመንግስት ያለው አመኔታ

(Citizens trust in Government )

ተፅዕኖ

(Impact) አጠቃቀም (Usage)

ዝግጁነት (Readiness)

Page 55: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

45

4.2.1 ዝግጁነት ከላይ እንደተጠቀሰው የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተፅዕኖ በመንግስት

አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደረውን ተፅዕኖ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ለመዳሰስ ተዛማጅ

የሆኑ ጉዳዮችን አብረን ተመልክተናል፡፡ የተቋማትን የኢኮቴ መሠረተ ልማት ዝርጋታን፣

የኢኮቴ ባለሙያውን፣ የሠራተኛውንና የኃላፊውን የኢኮቴ ዕውቀት ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

በክልሉ የወረዳኔትና ስኩልኔት ሽፋን አመርቂ ሲሆኑ በዚህ ረገድ የተሰራው ሥራ ሊበረታታ

ይገባል፡፡ በሌላ በኩል በLAN መሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በኢንተርኔት አገልግሎት

መሠረተ ልማቶች ሽፋን መካከለኛ በመሆኑ በዚህ ረገድ ብዙ መሠራት እንዳለበት

እንገነዘባለን፡፡ ያለውም LAN መሠረተ ልማት ዝርጋታ በክልል ቢሮዎች ካሉት በስተቀር

ደረጃውን የጠበቀ አይደለም፤ የኢንተርኔት አገልግሎትም ቢሆን በአብዛኛው የዲያል አፕ

ወይም CDMA ስለሆኑ ለተወሰኑ ሃላፊዎች ብቻ የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ የእነዚህ መሠረተ

ልማቶች ከፍተኛና ደረጃቸውን የጠበቁ አለመሆናቸውና በሰፊው አለመዳረስ ለቴክኖሎጂው

አጠቃቀም ድግግሞሽ መቀነስ እና የሚያስድሩትም ተፅዕኖ ዝቅተኛ መሆን የራሱ ድርሻ

ይኖረዋል፡፡ በተለይ የድረ ገፅ ሽፋን በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ዞንና ወረዳዎች የራሳቸውን

ድረ ገፅ እንዲያለሙ ይጠበቃል፡፡

በኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት ዙሪያ የኮምፒውተር ሠራተኛ ጥምርታ 1፡3 (1 ለ 3)

መሆኑና አጠቃላይ የኮምፒውተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት መካከለኛ

በመሆኑ አበረታች ነው ፡፡ ከላይ ከተጠቀሰው ዝቅተኛ የድረ ገፅ ሽፋን በተጨማሪ ያሉት

ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች እንዲሁም የባለቤትነት መብት ያላቸው አንቲቫይረሶች አቅርቦት

በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ አቅርቦቱን በማሻሻል በኩል ብዙ መሥራት ይጠበቃል ፡፡

ለኢኮቴ የተሰጠውን ትኩረት በተመለከተ ለኢኮቴ የሚመደብ የበጀት ድርሻ፣ ለባለሙያዎች

የተዘጋጀ ምቹ የሥራ ቦታ፣ እንዲሁም በኢኮቴ የሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲኖር የተደረገው

ጥረት የተሻለ ቢሆንም አፈፃፀሙ ዝቅተኛ ነው፡፡ በተለይ ኢኮቴን አስመልክቶ ጥናትና

ምርምር በማድረግ በኩል እንዲሁም ራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል እንዲኖር ከማድረግ አኳያ

ብዙ አልተሰራም ፡፡ ራሱን የቻለ ሰርቨር ሩም እና የሥልጠና ማዕከል የማዘጋጀት

እንዲሁም የቪዲዮ ኮንፈረንስ አዳራሽ ራሱን ችሎና በተገቢው ቁሣቁስ እንዲደራጅ

የማድረግ ሥራም ይቀረዋል፡፡

Page 56: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

46

የኢኮቴ ዕውቀትን ደግሞ ስንመለከት የኢኮቴ ባለሙያዎችን በተናጠል ብናይ ድረ ገጽ፣

ሶፍትዌርና ዳታ ቤዝ የማልማትና የማሻሻል ዕውቀት እንዲሁም አድቫንስድ የኮምፒውተር

ቋንቋ ዕውቀታቸው አነስተኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ የኢኮቴ መምህራንን በተመለከተ ከላይ

የተጠቀሱት እንደተጠበቁ ሆነው በተጨማሪ ቤተ ሙከራን የሚተካ ሲሙሌሽን የመጠቀም

ዕውቀት እንደዚሁ አናሳ ነው፡፡ በተለይ የአይ.ፒ ሜሴንጀር፣ ሜሴጅ ፖፕ አፕ፣ ኔትሚቲንግ

ወዘተ. የመጠቀም ዕውቀት በሠራተኛውና በኃላፊዎች የማዳበር ሥራ በጣም ብዙ

ይቀረዋል፡፡

4.2.2 አጠቃቀም የኢኮቴ ባለሙያው /የሥራ ሂደት አስተባባሪ፣ የሠራተኛው እና የበላይ ኃላፊው

ማይክሮሶፍት ወርድን በተደጋጋሚ እንደሚጠቀሙና አጠቃቀማቸውም ከሁሉም የተሻለ

ነው፤ በተቀራኒው አይ.ፒ ሜሴንጀር፣ ሜሴጅ ፖፕ አፕ፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ. በአብዛኛው

አይጠቀሙም፡፡ በተናጠል የኢኮቴ መምህራን የትምህርት መርጃ ሲሙሌሽን የሚጠቀሙት

አልፎ አልፎ ነው፡፡ በተጨማሪም ሠራተኛውንና ኃላፊዎችን በጋራ ብንመለከት ደግሞ

የማይክሮ ሶፍት አክሰስ፣ በLAN ዝርጋታ በመጠቀም ሀብትን መጋራትና መረጃ መለዋወጥ

እንዲሁም የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞችን የመጠቀም ሁኔታ አልፎ አልፎ የሚከናወን

ነው ፡፡

የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ መጠንን ብናይ ኮምፒውተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሳሪያዎችን

የሚጠቀመው አብዛኛው ባለሙያ፣ ሠራተኛና ኃላፊ ቢሆንም ሌሎች አገልግሎቶችን

የሚጠቀሙት ግን ጥቂት ናቸው፤ በተለይ የተቋሙን ድረ ገፅ ተጠቃሚ መጠን እና የቪዲዮ

ኮንፈረንስ ተጠቃሚ መጠን ዝቅተኛ ነው፡፡

Page 57: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

47

4.2.3. የኢኮቴ ተፅዕኖ

ሰንጠረዥ 34 - የኢኮቴ ተጽዕኖ በመንግስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እይታ ተ.ቁ

የኢኮቴ ተጽዕኖ

ባለሙያ ብዛት 200

ሰራተኛ ብዛት 399

የበላይ ሃላፊ ብዛት 245

አማካይ (Weighted Mean)

1 በአጠቃላይ ኢኮቴ ስራዬን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድቶኛል

4.55 4.17 4.21 4.27

2 ማይክሮሶፍት ወርድ ደብዳቤ፣ ዶክመንት ወዘተ.. ለማዘጋጀት ረድቶኛል

4.64 4.22 4.16 4.30

3 ማክሮሶፍት ኤክስል ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ.. ለማዘጋጀት ረድቶኛል

4.38 3.80 3.87 3.95

4 ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ ረድቶኛል

3.97 3.57 3.53 3.65

5 የላን ዝርጋታ መኖሩ ገብትን ጊዜንና ወጪን ቆጥቦልኛል

3.91 3.69 3.48 3.68

6 አይፒ ሚሴንጀር ኔት ሚቲንግ ወዘተ መጠቀም ሥራን ያቃልላል፣ ወጪንም ቆጥቧል

3.56 3.17 3.12 3.24

7 ወረዳኔት/ስኩል ኔት የተለያየ አገልግሎቶች በየአካባቢዉ እንዲዳረሱ በማድረግ ገንዘብ ጊዜና ጉልበትን ቆጥቧል

3.68 3.39 3.42 3.46

8 ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል

4.20 3.80 3.75 3.88

9 ኢኮቴ የመስመር ላይ ድጋፍ ለማድረግ/ለመቀበል ረድቶኛል

3.75 3.29 3.34 3.41

10 ኢኮቴ የስራ ተነሳሽነቴን ጨምሮልኛል 4.25 3.82 3.80 3.90 11 ኢኮቴ አንዳንድ ማቴሪያሎችን በነፃ

ለማግኘት አስችሎኛል 3.87 3.49 3.73 3.64

12 ኢኮቴ የአሰራር ዘዴን በማሻሻሉ ዉጣዉረድን አጥሯል

4.18 3.89 3.92 3.96

13 ኢኮቴ የሰራተኛዉን ብሎም የተቋሙን ስራ አፈፃጸም አሻሽሏል

4.03 3.80 3.80 3.85

14 ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ ልዉዉጥ በማከናወን ጊዜ፣ ጉልበት ወጪን ቆጥቧል

4.00 3.91 3.65 3.85

Page 58: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

48

የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ ኢኮቴ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደረውን ተፅዕኖ

መዳሰስ ነው፤ በዚህም ባለሙያዎች፣ ሠራተኞችና ኃላፊዎች በተስማሙት መሠረት

በሰንጠረዥ 34 እንደተመለከተው ኢኮቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ

አሳድሯል፡፡

ሥራን በፍጥነትና በጥራት ለመሥራት፣

ደብዳቤ፣ ዶክመንት፣ ቻርት፣ ፔሮል፣ ወዘተ. በቀላሉ ለማዘጋጀት፣

አስተማማኝ መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ፣

የአሠራር ዘዴን በማሻሻል ውጣ ውረድን ለማሳጠር፣

የሰራተኛውን ተነሳሽነት ለመጨመር፣

የሠራተኛውን ብሎም የተቋሙን ሥራ አፈፃፀም ለማሻሻል፣

ወረቀት አልባ የመረጃ ልውውጥ በማከናወን ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘብን ለመቆጠብ

አስችሏል፡፡

ለእነዚህ አዎንታዊ ተፅዕኖዎች በአጠቃላይ ኢኮቴ ምክንያት ቢሆንም የማይክሮሶፍት

ወርድ፣ ኤክስኤል፣ ኢንተርኔትና የላን ዝርጋታ ዋና ዋናዎቹ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ናቸው፤

ምንም አይነት ተፅዕኖ ያላደረጉ አይ.ፒ ሜሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ. ናቸው፡፡ በሌላ

በኩል ከተቋማት ደንበኞች በተሰበሰበ መረጃ ኢኮቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ አወንታዊ

ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡

አገልግሎት አሠጣጡ ቀልጣፋና ውጤታማ መሆኑ፣

አገልግሎት አሠጣጡ ደንበኛን ማርካቱ፣

አገልግሎት አሰጣጡ በየአካባቢው ተዳርሶ ጊዜ፣ ጉልበትና ወጭ መቆጠቡ፣

አገልግሎት አሠጣጡ ግልጽና ፍትሃዊ መሆኑ፣

የመ/ቤቱ መረጃ አያያዝና አደረጃጀት መሻሻሉ፤

በሌላ በኩል በሰራተኛው የስራ ተነሳሽነት በመጨመር ላይ በደንበኛው እይታ ምንም

አይነት ተጽዕኖ አላሳደረም፡፡ ነገር ግን ከጠቅላላው ተጠኝዎች ጋር በአማካይ ሲሰላ ኢኮቴ

የሰራተኛውን የስራ ተነሳሽነት መጨመሩን ማረጋገጥ ይቻላል፡፡

በአጠቃላይ በአማካይ ኢኮቴ ምንም አይነት አሉታዊ / ኔጌቲቭ/ ተፅዕኖ አላሳደረም፤ ይህም

ማለት በአማራ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ኢኮቴ አዎንታዊ / ፖዘቲቭ/

ተፅዕኖ አሳድሯል ብሎ መደምደም ይቻላል፤ የጥናቱ ውጤትም ይህ ነው ፡፡

Page 59: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

49

4.2.4 የዝግጁነት፣ አጠቃቀም እና ተፅዕኖ ኮሪሌሽን

ሮቢን እንደሚለው ዝግጁነት፣ አጠቃቀም እና ተፅዕኖ ፖዘቲቭ (አዎንታዊ) ኮሪሌሽን

አላቸው፡፡ በዚህ ጥናትም የተረጋገጠው ይህ ነው፡፡ በምሳሌነት የማይክሮሶፍት ወርድ

እውቀት ከአጠቃቀም እንዲሁም የማይክሮሶፍት አጠቃቀም ከተፅዕኖ ጋር አዎንታዊ

ኮሪሌሽን እንዳላቸው አይተናል፡፡ ስለዚህ ኢኮቴ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ አዎንታዊ

ተፅዕኖ እንዲያመጣ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የኢኮቴ ዕውቀት ከፍተኛ መሆኑና

የተገልጋዮቹ አጠቃቀም በተደጋጋሚ መሆኑ ነው፡፡ ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃን በቀላሉ

ለማግኘትና ለመለዋወጥ ያስቻለው የኢንተርኔትና የመረጃ መበርበሪያ (search engine)

ዕውቀትና አጠቃቀም የተሻለ በመሆኑ ነው፡፡ አጠቃላይ ኢኮቴ በአገልግሎት አሰጣጡ

ላይ ተፅዕኖ ለማሳደሩ የኢኮቴ ዕውቀት እና አጠቃቀም ከፍተኛ አስተዋፅኦ አላቸው፡፡

የኢኮቴ ስልጠና በሌላ በኩል አዎንታዊ ኮሪሌሽን ከተፅዕኖ ጋር ሲኖረው የትምህርት

ደረጃና የሥራ ልምድ በተቃራኒው ምንም ወይም የተቃርኖ ኮሪሌሽን አላቸው ፡፡

Page 60: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

50

ምዕራፍ አምስት

5. የጥናቱ ውጤት መደምደሚያና የመፍትሄ ሃሳብ

5.1. የጥናቱ ውጤት መደምደሚያ በአማራ ክልል ኢኮቴ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሳደረዉን ተፅዕኖ ለመቃኘት

በተደረገ ጥናት የኢኮቴ ዕቃዎች አቅርቦት፣ የኢኮቴ አገልግሎት ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን፣

ለኢኮቴ የተሰጠዉን ትኩረት፣ የባለሙያዉ የሰራተኛውና የኃላፊዉ የኢኮቴ ዕዉቀት

አጠቃቀም እንዲሁም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሳደረዉን ተፅዕኖ ዉጤት

እንደሚከተለው ከፋፍለን እንደመድማለን፡፡

o የኢኮቴና ተዛማጅ ዕቃዎች አቅርቦት

የኮምፒዩተር - ሠራተኛ ጥምርታ የኮምፒዩተር አቅርቦት ምን እንደሚመስል ለመለካት

ይረዳናል(መስፍን ገ/ማርያም፣2004 እ.ኤ.አ.)፡፡ በዚህ ጥናትም የኮምፒዩተር አቅርቦት

መካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሌሎች ተዛማጅ ዕቃዎችን ጨምሮ የባለቤትነት መብት

ያላቸዉ አንቲ ቫይረሶች አቅርቦት ዝቅተኛ ነዉ፡፡

o የኢኮቴ መሰረተ ልማት ሽፋን

የወረዳኔት እና የስኩል ኔት ሽፋን ከፍተኛ መሆኑን ስንረዳ ኢንተርኔት፣ የLAN ዝርጋታ፣

የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች ሽፋን መካከለኛ ሲሆን የድረ-ገጽ ሽፋን ደግሞ ዝቅተኛ

ነዉ፡፡

o ለኢኮቴ የተሰጠ ትኩረት

በአጠቃላይ ለኢኮቴ የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ ነው፤ በተለይ በተቋማት ኢኮቴን

አስመልክቶ የተደረገ ጥናትና ምርምር በጣም አነስተኛ ነው፡፡ ራሱን የቻለ ሰርቨር ሩም

አለመኖር፣የጥገና ማዕከላትና የስልጠና ማዕከል አለመኖር ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ የጥገና

ማዕከላትን አስመልክቶ በተቋሙ መቋቋም አለባቸው ወይም ለግልዘርፉ መሰጠት አለባቸው

የሚለው አዋጭነቱ በተጨማሪ ጥናቶች መመለስ አለበት፡፡

o ኢኮቴ/ተዛማጅ ስልጠና

በኢኮቴና ተዛማጅ የመሰረታዊ ኮምፒውተር አጫጭር ስልጠና ወስደው ማስረጃ ያላቸው

ሰራተኞችና ሃላፊዎች ቁጥር አነስተኛ ነው፡፡

Page 61: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

51

o የኢኮቴን አገልግሎት ማዳረስ

በአብዛኛዉ ሠራተኛ፣ ባለሙያ እና የበላይ ኃላፊ የኢኮቴ አገልግሎት በመንግስት ተቋማት፣

እንደ ኢንተርኔት ካፌ ያሉ መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት አገልግሎቱን ሲያገኙ ዝቅተኛ

ቁጥር ያለዉ የመንግስት ሠራተኛ እቤቱ ድረስ አገልግሎቱን ያገኛል፡፡

o የኢኮቴ ዕዉቀት

የኢኮቴ ባለሙያዉ የማክሮሶፍት ወርድ ዕዉቀት ከፍተኛ ሲሆን የበላይ ኃላፊዉና

የሰራተኛዉ ግን መካከለኛ ነዉ፡፡ በተቃራኒዉ የባለሙያዉ የኮምፒዩተር ቋንቋ (advanced

computer language)፣ ድረ ገጽና ዳታ ቤዝ የማልማት ዕዉቀት ግን ዝቅተኛ ነዉ፡፡

የኢኮቴ መምህራን በተናጠል የትምህርት መረጃ ሲሙሌሽን አጠቃቀም ዕዉቀት እንደዚሁ

ዝቅተኛ ነዉ፡፡ የሰራተኛዉና የበላይ ኃላፊዉ ማይክሮሶፍት ኤክሴል፣ ተደራሽነት፣

ፓወርፖይንት፣ ኢ-ሜይል መላላክ፣ እንደ ጎግል ያሉ የመረጃ መበርበሪያ (search engine)

እና በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-መፃህፍት የአጠቃቀም ዕዉቀት ዝቅተኛ ሲሆን በተለይ

የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች እንዲሁም አይ.ፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ. ያሉ

ላንቱል የመጠቀም ዕዉቀት በጣም ዝቅተኛ ነዉ፡፡

o የኢኮቴ አጠቃቀም

አብዛኛዉ የተቋማቱ ሠራተኞች የኮምፒዩተርና ተዛማጅ የኢኮቴ ዕቃዎች /መሳሪያዎች

ተጠቃሚ ሲሆኑ ኢንተርኔት፣ ወረዳኔት ወይም ስኩል ኔት፣ የLAN መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣

የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ተጠቃሚ ሰራተኞች ግን ጥቂት

ናቸዉ፡፡ የተቋማቸውን ድረ-ገጽ የሚጠቀሙ ደግሞ በጣም ጥቂቶች ናቸዉ፡፡

የኢኮቴ መምህሩ የሲሙሌሽን አጠቃቀም አልፎ አልፎ ሲሆን በአጠቃላይ የኢኮቴ

ባለሙያዉ የማይክሮሶፍት ወርድ አጠቃቀም ሁልጊዜ ነው፤ የሰራተኛዉና የበላይ ኃላፊዉ

ደግሞ በተደጋጋሚ ነዉ፡፡ የኢኮቴ ባለሙያዉ የአይ.ፒ ሚሴንጀርና ኔትሚቲንግ አጠቃቀም

አልፎ አልፎ ነው፡፡ አብዛኛዉ ኃላፊና ሠራተኛ አይ.ፒ ሜሴንጀርና ኔትሚቲንግ

አይጠቀምም ማለት ይቻላል፡፡ ማክሮሶፍት ኤክሴል፣ ፓወር ፖይንት፣ ኢ-ሜይል መላላክ፣

እንደ ጎግል ያሉ የመረጃ መበርበሪያ (search engine) እና በCD/RAM የተቀመጡ ኢ-

መፃህፍት፣ የLAN መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞችን አልፎ አልፎ

ይጠቀማሉ፡፡

Page 62: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

52

o የኢኮቴ ተፅዕኖ

በአጠቃላይ ከሰራተኛዉ፣ ከበላይ ኃላፊና ከኢኮቴ ባለሙያ በተሰበሰበ መረጃ መሰረት ኢኮቴ

ለአገልግሎት አሰጣጥ ፍጥነትና ጥራት መሻሻል፣ ዉጣ ዉረድን በመቀነስ፣ ደብዳቤ፣

ዶክመንት፣ ቻርት፣ ፔሮል ወዘተ. በቀላሉ ለማዘጋጀት አስችሏል፡፡ ይህም አስተማማኝ

መረጃን በቀላሉ በማግኘትና በመለዋወጥ ሀብት፣ ጉልበት፣ ጊዜና ወጪን በመቆጠብ ወረቀት

አልባ የመረጃ ልዉዉጥ በማከናወን፣ የሰራተኛዉን ተነሳሽነት በመጨመር እንዲሁም

የሰራተኛዉንና የተቋሙን ሥራ አፈፃፀም በማሻሻል አዎንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡

ማይክሮሶፍት ወርድ፣ ማይክሮሶፍት ኤክሴል፣ ኢንተርኔትና የ LAN መሰረተ ልማት

ዝርጋታ ዋና ዋናዎቹ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ናቸዉ፡፡ በአንጻሩ ደግሞ የቀጥታ የመስመር ላይ

ድጋፍ ለማድረግ ወይም ለመቀበል፣ በርቀት ዴስክቶፕ መረጃ ለመለዋወጥ፣ ኢኮቴ የተለያዩ

ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን በየአካባቢዉ በማድረስ ገንዘብ፣ ጊዜና ጉልበት በመቀነስ ረገድ

ምንም አይነት ተፅዕኖ አላሳደረም፤ በዚህ በኩል አይ.ፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ.

የመሳሰሉ የርቀት ዴስክቶፕ ላን ቱሎች፣ የወረዳኔትና ስኩል ኔት አገልግሎቶች ተጠቃሾች

ናቸዉ፡፡

የአገልግሎት አሰጣጡን ግብረ መልስ ከደንበኛዉ አይን መቃኘት አስፈላጊ በመሆኑ ይህን

ታሳቢ በማድረግ ከደንበኞች በተሰበሰበዉ መረጃ መሰረት የመንግስት አገልግሎት አሰጣጡ

ቀልጣፋ፤ ዉጤታማ፤ ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ መቆጠቡ፤ ግልጽና ፍትሀዊ መሆኑ፤

በአጠቃላይ የመረጃ አያያዝና አደረጃጀቱ በመሻሻሉ አወንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡

የመስሪያ ቤቱን ሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት በተመለከተም እንደዚሁ ከሁሉም ተጠኝዎች

ጋር በአማካይ ሲሰላ አዎንታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ተረጋግጧል፡፡ በይበልጥ በደንበኛዉ

እርካታ ረገድ ኢኮቴ አዎንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡

በአጠቃላይ ኢኮቴ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በአማካይ አዎንታዊ ተፅዕኖ

አሳድሯል ብሎ መደምደም ይቻላል፡፡

5.2. የመፍትሄ ሃሳቦች o አንድ ኮምፒዩተር ለሶስት ሠራተኞች እያገለገለ እንደሆነ አይተናል፡፡ ስለዚህ የተሻለ

ጥምርታ ወይም ጥምርታዉን ለመቀነስ ኤጀንሲዉ ከተቋማቱ እና ለዘርፉ ድጋፍ

ከሚሰጡ አካላት ጋር በመተባበር ተጨማሪ ኮምፒዩተሮች የሚገኙበትንና

ለአገልግሎት የሚውሉበትን መንገድ ማፈላለግ ይኖርበታል፤ ሌሎች ተዛማጅ የኢኮቴ

Page 63: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

53

ዕቃዎችም በተመሳሳይ መፍትሄ ያሻቸዋል፤ የባለቤትነት መብት ያላቸዉ አንቲ-

ቫይረሶች በበቂ መጠን መሰራጨት ይኖርባቸዋል፡፡

የኮምፒውተር እጥረትን ለመቅረፍ PC-Station በመጠቀም አንድን ሲስተም ዩኒት

በተለያዩ ሞኒተሮች በተመሳሳይ ሰዓት ለመጠቀም ያስችላል፡፡ የሚያስገኘው ጥቅምም

ወጭን መቀነስ፣ ቡዙ ኮምፒተሮችን ከማስተዳደር በቀላሉ አንድ የተሻለ

ኮምፒዩተርን በመጠቀም ለማስተዳደር ያስችላል፡፡ በመሆኑም ሲስተሙን

የኢንተርኔት እና የስልጠና አገልግሎት በሚሰጡ ማዕከላት ላይ መጠቀም

ይመከራል፡፡

o የኢኮቴ ተደራሽነት ሁሉም እንዲያገኙ የኢኮቴ ተቋማትን በቁሳቁስ ከማደራጀት ጎን

ለጎን ሁለገብ የማህበረሰብ መረጃ አገልግሎት ተቋማትንና እንደ ኢንተርኔት ካፌ

ያሉ የግል ተቋማትን ማበረታታት ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ሁለገብ የማህበረሰብ መረጃ

ማዕከላትን የኢንተርኔትና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ማገዝ ይገባል፡፡ በዚህ

ረገድ በቅርቡ ኤጀንሲዉ CDMA-1x በመግዛት ለሁለገብ የማህበረሰብ መረጃ

ማዕከላቱ ማከፋፈሉ ሊበረታታ ይገባል፡፡ እነዚህ ተቋማት (መንግስታዊና መንግስታዊ

ያልሆኑ) በዘላቂነት የብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት በተመጣጣኝ ዋጋ

እንዲያገኙ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት በመስራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ

የክልሉን የኢንተርኔት ሽፋን ለማሳደግ ብሎም የክልሉን የመንግስት አገልግሎት

አሰጣጥ ለማሻሻል ቁልፍ ሚና ይኖረዋል፡፡

o በወረዳኔትና ስኩል ኔት የተለያዩ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን በየአካባቢዉ በማድረስ

በኩል ለአገልግሎት አሰጣጡ ያሳደሩት ተፅዕኖ የለም፡፡ እንደሚታወቀዉ በወረዳኔት

አገልግሎት የሚካተቱ አገልግሎቶች የቪዲዮ ኮንፈረንስ፣ ኢንተርኔትና አይ.ፒ

ቴሌፎን ናቸዉ፤ ነገር ግን እስካሁን በማገልገል ላይ ያለዉ ቪዲዮ ኮንፈረንስ ብቻ

ነዉ ማለት ይቻላል፡፡ ስኩልኔትም እንደዚሁ የሳተላይት ትምህርት አገልግሎት ብቻ

እየሰጠ ይገኛል፡፡ ከዚህ አኳያ ኢንተርኔት አገልግሎት በእነዚህ አገልግሎቶች

ቢታገዝ ብቻ ያለዉን የኢንተርኔት ሽፋን በጣም ማሳደግ ይቻላል፡፡ በቅርቡ

እየተከናወነ ያለዉ የወረዳኔትን ከVSAT ወደ ላንድ ላይን የመቀየር ስራ ሲጠናቀቅ

ይህንን ችግር የሚቀርፍ ሲሆን ስኩልኔትም በተመሳሳይ ወደ ላንድ ላይን ቢቀየር

የኢንተርኔትን ባንድ ዊድዝን ከማሳደግና ፍጥነቱን ከማሻሻል በተጨማሪ

Page 64: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

54

የኢንተርኔትን ሽፋን ለማሻሻል ምን ያህል ጠቀሜታ እንደሚኖረዉ መገመት

ይቻላል፡፡ በመሆኑም እዚህ ላይ ትኩረት ሠጥቶ መስራት ያሻል፤ በፌዴራል ደረጃም

የመገናኛና መረጃ ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን መፍትሄ

ሊፈልግለት ይገባል፡፡

o የኢንተርኔትና የLAN መሰረተ ልማት ዝርጋታ ሽፋን በአንፃራዊ የተሻለ ቢሆንም

ብዙ መስራት ይገባል፡፡ በተለይ ዞንና ወረዳዎችን የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት

አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ እንዲሁም የLAN መሰረተ ልማት ዝርጋታዉ

ደረጃዉን የጠበቀ እንዲሆን በማድረግ ሽፋኑን ማሳደግ ይገባል፡፡ በዚህ ረገድ በቅርቡ

በ52 ሴክተር መስሪያ ቤቶች የWLAN መሰረተ ልማት በዋየርለስ ለመዘርጋት

እየተደረገ ያለው ጥረት ሽፋኑን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡

o የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታቤዞችን በመጠቀም በኩል ለነጋዴው ህብረተሰብ የግብር

ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN Number) ለመስጠት በአብክመ ገቢዎች ባለስልጣን

ተግባራዊ የሆነው ዌብ ቤዝድ ዳታ ቤዝ (SIGTAS) በምሳሌነት ማንሳት ብቻ በቂ

ነው፡፡

ሲግታስ - የታክስ ስርዓት የሚሰጠው አገልግሎት የተቀናጀ የመንግስት የታክስ

አስተዳደር ስርዓት ነው፡፡ ለግብር ከፋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት ካስገኝው ጠቀሜታ

ባሻገር ሌሎችንም የግብር አይነቶች ለማስተዳደር የሚያስችል አቅም አለው፡፡

ሲግታስ በኤሌክትሮኒክ ፋይሊንግ የታገዘና ግብር ከፋዮች ኢንተርኔትን በመጠቀም

ግብራቸውን እንዲያሳውቁ የሚያደርግ ሲስተም ነው፡፡ ስልሆነም ሲስተሙን

በክልላችን በስፋት በመጠቀም ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው በግብር ከፋይ መለያ

ቁጥራቸው አማካይነት ግብር በአግባባቡ እንዲከፍሉ ለማድረግ ያስችላል፡፡

የገበያ ዋጋ መረጃ

የምርት ገበያ መረጃ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ለህብረተሰቡ ማሳወቅ ይቻላል

የስልክ አጭር መልዕክት፤ በሬዲዮና ቴሌቪዥን፡፡ እነዚህ የቴክኖሎጂ ውጤቶች

ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች ላሉ አርሶአደሮች ተደራሽ ለማድረግ የኤሌክትሮኒክ

የገበያ ዋጋ ሰሌዳዎች በዋና ዋና የገበያ ማዕከላትም ቢተከሉ ጠቃሚ ነው፡፡

Page 65: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

55

የትራፊክ ህግ ማስተማሪያ

ሲስተሙ የትራፊክ መገለጫ ምስሎችን ከነማብራሪያቸው የሚያሳይ ነው፡፡

በተጨማሪም የመኪና አሽከርካሪዎች የፈተና መፈተኛ ሲስተም አለው፡፡ በመሆኑም

ሶፍትዌሩን በመጠቀምና የትራፊክ መገለጫ ምስሎችን ከነማብራሪያቸው በማወቅ

የትራፊክ አደጋን መከላከል ይቻላል፡፡

የቋሚ ንብረት አስተዳደርና ክትትል

የመስሪያ ቤቶች ቋሚ ንብረት አስተዳደር በቴክኖሎጅ የተደገፈ ሆኖ የቋሚ

ንብረቶችን ክትትልና ቁጥጥር ወደ አስተማማኝ ደረጃ ያሳደገ በባር ኮድ የታገዘ

የንብረት ክትትል ሲስተም ነው፡፡ ሲስተሙ ንብረትን ከብክነት በመከላከል በኩል

ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡

የሰው ሃይል አስተዳደር

ይህ ዘዴ የተቋሙን ሰራተኞች ሙሉ መረጃ የሚይዝ ነው፡፡ ዳታቤዙን በመጠቀም

የሰራተኞችን መረጃ በአስተማማኝ ሁኔታ ለመያዝና ሲፈለግም ጥቅም ላይ ለማዋል

ያስችላል፡፡

በተጨማሪም Drag Store Management System, Health license

Management System, Online library catalog system, የከፍተኛ ትምህርት

ተቋማት ተማሪዎች ምዝገባና ውጤት ማሳወቂያ ወዘተ. ሶፍትዌሮች

በሚመለከታቸው የክልላችን መስሪያ ቤቶች ጥቅም ላይ ቢውሉ የአገልግሎት

አሰጣጣቸውን በእጅጉ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚኖራቸው ሚና የላቀ

ነው፡፡

ሁሉም ተጠኝዎች እንደሚስማሙት የሁሉም ተቋማት በየአስተዳደር እርከኑ ወረዳ ከዞን፣

ዞን ከክልል እንዲሁም ሴክተር ከሴክተር መረጃ ልዉዉጣቸዉና ሪፖርት አላላካቸው

በወረዳኔት ወይም ስኩል ኔት መታገዝ አለበት፡፡ በሁሉም ዘርፎችና አገልግሎቶች ግብርና፣

ጤና፣ ገቢዎች፣ አካባቢ ጥበቃና መሬት አስተዳደር፣ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት፣ ትምህርት

ወዘተ. ላይ ተግባራዊ ሊሆን ይገባል፡፡

Page 66: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

56

የድረ ገጽ ሽፋንን በተለይ በዞንና ወረዳ ደረጃ ለማሳደግ ልማቱን በኤጀንሲዉ

ባለሙያዎች ብቻ ማከናወን አይጠበቅም፡፡ ስለዚህ የዞንና የወረዳ ኢኮቴ

ባለሙያዎችን አቅም በስልጠና አዳብሮ ሽፋኑ እንዲሻሻል ንቅናቄ ማድረግ

ይጠበቃል፡፡ በዚህ ረገድ በቅርቡ በኤጀንሲዉ አዘጋጅነት ክልል ላይ የተሰጠዉ

የአሰልጣኞች ስልጠና ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ በድረ ገጽና ዳታ ቤዝ

ልማት ጠቀሜታ ዙሪያም የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ በዞንና ወረዳ በስፋት መሰራት

አለበት፡፡

ለኢኮቴ ተፅዕኖ አጠቃቀሙን ማሳደግ፤ አጠቃቀሙን ለማሳደግ ደግሞ ባለሙያዎች

ብሎም ሁሉም ሠራተኞች ክህሎቱ እንዲኖራቸዉ ማድረግ፤ የዕዉቀት አጠቃቀምና

ተፅዕኖ ኮርሌሽን እንዳላቸዉ እንደዚሁ ለተፅዕኖ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ

ሳይሆን ስልጠና ኮርሌሽን እንዳለዉ በዚህ ጥናት ተረጋግጧል፡፡ በአጫጭር የኢኮቴ

ስልጠና በሚገኝ እውቀት ብቻ ብዙ አመት የስራ ልምድና የትምህርት ደረጃ

ሳይጠይቅ የአገልግሎት አሰጣጡን ማሻሻል እንደሚቻል ታይቷል፡፡ ከዚህ ጋር

ተያይዞ ለኢኮቴ ባለሙያዉ በተናጠል የአድቫንስድ ኮምፒዩተር ቋንቋ ስልጠና፣

ለኢኮቴ መምህራን የትም/መረጃ ሲሙሌሽን ትዉዉቅና አጠቃቀም ስልጠና መስጠት

ያሻል፡፡ በተለይ አይፒ ሚሴንጀር ኔትሚቲንግ ወዘተ. የመሳሰሉ ላን ቱልስ

የአጠቃቀም ማንዋል ማዘጋጀት ሁሉንም የተቋሙን ማህበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጥ

ማስተዋወቅና ማሰልጠን እንዲሁም ተግባራዊ መደረጉን መከታተል ያስፈልጋል፡፡

በኢኮቴና ተዛማጅ (የመሰረታዊ ኮምፒዩተር) አጫጭር ስልጠና ወስደዉ ማስረጃ

ያላቸዉ ሠራተኞችና ኃላፊዎች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ወደፊት ለአመራሩና

ሰራተኛው የመሰረታዊ ኮምፒዩተርና ሌሎች አጫጭር ስልጠናዎች በየአስተዳደር

እርከኑ ማዘጋጀትና መሥጠት የግድ ይላል፡፡

ለኢኮቴ የተሰጠ ትኩረት በአጠቃላይ አነስተኛ ነዉ፡፡ ለኢኮቴ የሚመደብን የበጀት

ድርሻ ከፍ ማድረግ፣ ለባለሙያዎች ምች የስራ ቦታ መስጠት፣ ተቋማት የራሳቸው

የኢኮቴ ማሰልጠኛ እንዲኖራቸው ማድረግ፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ አዳራሽ በተገቢው

ቁሳቁስ እንዲደራጁና ለተገቢው አገልግሎት እንዲውሉ ማድረግ ወዘተ. ችላ ሊባሉ

አይገባም፡፡

Page 67: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

57

የኢኮቴ ተፅዕኖን በተመለከተ ኢኮቴ የመስመር ላይ ድጋፍ ለማድረግ ወይም

ለመቀበል ያሳደረዉ ተፅዕኖ ባለመኖሩ ይህንን ለማሻሻል የሚያስችሉ አገልግሎቶችን

ለምሳሌ የርቀት ዴስክቶፕ በመጋራት፤ የLAN መሰረተ ልማት ደረጃዉን የጠበቀ

ሆኖ እንዲዘረጋና እንዲዳረስ በማድረግ፤ አይ.ፒ ሚሴንጀር፣ ኔትሚቲንግ ወዘተ.

የመሳሰሉ የLAN ቱል ሶፍትዌሮችን በማስተዋወቅ፣ ከኢንተርኔት በማዉረድ ወይም

አክቲቬት በማድረግ፣ የአጠቃቀም ማንዋል በማዘጋጀት እና እንዲጠቀሙ በማድረግ፤

የወረዳኔት እና ስኩል ኔት አገልግሎትን ተጠቅሞ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ልምድ

ልዉዉጥ በማድረግ ከችሎትና ከሳተላይት ትምህርት አገልግሎት በተጨማሪ

ለሌሎች ዘርፈ ብዙ አገልገሎቶች በማዋል አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ተፅዕኖ

እንዲያሳድሩ ማድረግ ይገባል፡፡

ወረዳኔት ለችሎት አገልግሎት መጠቀም ከተጀመረ ዉሎ አድሯል፡፡ ይህ አበረታች

ቢሆንም ሌሎች ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች ከመኖራቸዉ አንፃር ብዙ መስራት

ይቻላል፡፡ ለምሳሌ የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አሰጣጥ በቅርቡ ለመጀመርና የንግዱ

ህብረተሰብ በየአካባቢዉ የመስመር ላይ ምዝገባና ፍቃድ እንዲያገኝ እየተደረገ

ያለዉን ጥረት ብቻ ማንሳት በቂ ነዉ፡፡ እንደሮቢን ገለፃ ለህብረተሰቡ ሁሉንም

አገልግሎቶች በመስመር ላይ በአቅራቢያዉና አካባቢዉ ማዳረስ (online service

provision) የደንበኛዉ እርካታ ከመጨመር አንስቶ ህዝቡ ለመንግስት ያለዉን

አመኔታ እስከማሻሻል ይደርሳል፡፡ በአጠቃላይ ኢኮቴ በመንግስት አገልግሎት

አሰጣጥ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዲያደርግ ይረዱታል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ

በወረዳኔትና ስኩል ኔት አገልግሎት ላይ የባለሙያዉን ክህሎት ማዳበር፣ በብልሽት

ወቅት በራሱ ችግሩን እንዲፈታና እንዲጠግን አገልግሎቱን ለተለያየ አገልግሎት

እንዲያዉል ማሰልጠን ጠቃሚ ነዉ፡፡ በዚህ ረገድ ኤጀንሲዉ በቅርቡ የሠጠው

የወረዳኔት፣ ስኩልኔትና የገጠር ሽቦ አልባ ስልክ የአሰልጣኞች ስልጠና ጉልህ

አስተዋጽ ይኖረዋል፡፡

የወረዳኔት አይ.ፒ ቴሌፎን አገልግሎትን ማስጀመርምና በአገባቡ ለአገልግሎት

ማዋል ችላ የማይባል ጉዳይ ሊሆን ይገባዋል፡፡

Page 68: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

58

በአጠቃላይ በኤጀንሲያችን ማቋቋሚያ ደንብ ቁጥር እንደተመለከተዉና ሁሉም መልስ

ሰጭዎች እንደሚስማሙበት ከክልል እስከ ወረዳ ብሎም እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ ተቋማትና

አገልግሎቶች ኦቶሜት መደረግ አለባቸዉ፡፡ በዚህ ረገድ ኤጀንሲዉ እያስለማ ያለዉ

የቢ.ፒ.አር ኦቶሜሽን ትልቅ ተግባር ነው፤ ይህ ተግባር የድረ ገጽና ኢንተርኔት ሽፋንን

ለማሳደግ እንዲሁም አገልግሎትን በመስመር ላይ የመስጠት ተግባርን ለማከናወን መሰረት

ነው፡፡

በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዘርፍ በተለይም በክልላችን በቂ ጥናትና ምርምር

አልተካሄደም፡፡ በመሆኑም በዘርፉ የተለያዩ ይዘቶችን እያነሱ ሰፊ ጥናትና ምርምር ማድረግ

ያስፈልጋል፡፡ የጥናት ቡድኑም ከዚህ በታች ለአብነት በተዘረዘሩ ይዘቶች ላይ በክልላችን ጥናትና

ምርምሮች እንዲካሄዱ ይመክራል፡፡

1) የኢኮቴ ቁሳቁሶች የጥገና ማዕከል በየተቋማቱ መቋቋም አለበት ወይስ ለግሉ ዘርፍ

መሰጠት አለበት? በሚል የአዋጭነት ጥናት ቢካሄድ

2) “Return on ICT Investment” አመልካቾች ተቀምጠውለት ዝርዝር ጥናት

ቢካሄድበት

3) የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመልካም አስተዳደር፣ በጤና፣ በትምህርት፣

በግብርና፣ እና በሌሎች ሴክተሮች ላይ ያለው ተጽዕኖ ከየሴክተሮች ባህሪ አንጻር ጥናት

ቢደረግበት

Page 69: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

ዋቢዎች

1) የኢፌዲሪ ብሄራዊ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር፣ የኢፌዲሪ ብሄራዊ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ ፖሊሲና ስትራቴጅ ፣አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 2001 ዓ.ም፣

2) የአብክመ ምክር ቤት፣ ዝክረ ህግ ጋዜጣ ደንብ ቁጥር 72/2002 ዓ.ም፣ ባህር ዳር፣

ታህሳስ 2002 ዓ.ም

3) Fikre Y. Wondimu, ICT Infrastructure Survey for Amhara National Regional State, Addis Ababa, April 2004.

4) MuthuKrishnan and others, E Government Interoperability Framework for Ethiopia, Addis Ababa, December 2009.

5) Subhas Bhatnager, Impact Assessement Study of Computerized Service Delivery Projects from Indian and Chile, India, June 2007.

6) University of Siegen, Study on the Social Impact of ICT, Final Report, Germany, April 2010.

7) Gebremariam Mesfin, Integration of Computer Assisted Learning in to the Curricula of Ethiopian Schools, Thesis of Master of Scince in Computer Science, AAU, 2004.

8) Roben te Valde, Measuring the Impact of ICT on Public Sector Performance, July 2011.

9) Rob Johns, Likert Items and Scales, Survey Question Bank, University of

Strathclyde, March, 2010.

Page 70: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

አባሪ 1 በጥናቱ የተካተቱ መስሪያ ቤቶች ዝርዝር

ተ.ቁ የተጠኝው ምድብ የተመረጠው መ/ቤት

ጠቅላላ የተጠኝዎች ብዛት

ምርመራ

1 ክልል መ/ቤቶች

1. ትምህርት ቢሮ

150

ከእያንዳንዱ ቢሮ አስር ተጠኝዎች ይካተታሉ፡፡

2. ጠቅላይ ፍርድ ቤት 3. ፍትህ ቢሮ 4. ባህል፣ቱሪዝም ፓርኮች ልማት ቢሮ 5. ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ 6. ገቢዎች ባለስልጣን 7. ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ 8. ጤና ጥበቃ ቢሮ

9. ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ 10. ግብርና ቢሮ 11. ሴቶች፣ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ 12. ርዕሰ መስተዳድርና ክልል

መስተዳድር ም/ቤት ጽ/ቤት 13. ብዙሃን መገናኛ ኤጀንሲ 14. ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ

መከ/መቆ/ማስ/ጽ/ቤት 15. አካባቢ ጥበቃና መሬት አስ/አጠ/ ቢሮ

2

ዞንና ከተማ አስተዳደር (አስሩ ዞኖችና ሶስቱ ከተማ አስተዳደሮች)

1) ትምህርት መምሪያ

650

በሁሉም( አስር) ዞኖችና በሶስቱ ከተማ አስተዳደሮች በእያንዳንዱ መስሪያ ቤት አምስት አምስት ተጠኝዎች በድምሩ በአንድ ዞን (ከተማ አስተዳደር) 50 ተጠኝዎች ይካተታሉ፡፡

2) ከፍተኛ ፍርድ ቤት

3) ፍትህ መምሪያ

4) ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ 5) ገቢዎች

6) ጤና መምሪያ 7) ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ 8) ግብርና መምሪያ 9) ሴቶች፣ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ

መምሪያ 10) አስተዳደር ጽ/ቤት

3 ወረዳዎች

1) ትምህርት ጽ/ቤት 544 በ34 ወረዳዎች ከእያንዳንዱ ወረዳ 16 ተጠኝዎች ይካተቱበታል

2) ፍርድ ቤት 3) ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት 4) አስተዳደር ጽ/ቤት

ጠቅላላ ድምር 1344

Page 71: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

አባሪ 2 በጥናቱ የተካተቱ ዞንና ወረዳዎች ዝርዝር

ተ.ቁ ዞን/ ከተማ አስተዳደር ወረዳ / ከተማ አስተዳደር ምርመራ 1

ሰሜን ጎንደር

ደባርቅ

በእያንዳንዱ ወረዳ በተመረጡት አራት ጽ/ቤቶች በእያንዳንዳቸው አራት አራት ተጠኝዎች ይካተታሉ፡፡

አይከል ከተማ አስተዳደር ጎንደር ዙሪያ ደንቢያ

2

ደቡብ ጎንደር

ሊቦ ከምከም ወረታ ከተማ አስተዳደር ላይ ጋይንት

3

ዋግ ኸምራ ብሄረሰብ ዞን ሰቆጣ ዙሪያ አበርገሌ

4 ሰሜን ወሎ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር መቄት ዋድላ

5

ደቡብ ወሎ

አልቡኮ ቃሉ ሐይቅ ከተማ አስተዳደር

አምባሰል ኩታ በር

6

ኦሮሞ ብሄረሰብ

አርጡማ ፉርሲ ባቲ

7

ሰሜን ሸዋ

አንጾኪያ ገምዛ ሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር አንጎለላና ጠራ አንኮበር ሲያ ደብርና ዋዩ

8 አዊ ብሄረሰብ ዞን ዳንግላ ከተማ አስተዳደር አንከሻ ጓጉሳ

9 ምስራቅ ጎጃም

ማቻከል ደጀን ቢቸና ከተማ አስተዳደር ሁለት እጁ እነሴ

10 ምዕራብ ጎጃም

ፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ሰከላ ወንበርማ

ደምበጫ 11 ጎንደር ከተማ አስተዳደር

12 ደሴ ከተማ አስተዳደር 13 ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር

Page 72: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

1

አባሪ 3

መጠይቅ 1.በኢኮቴ ባለሙያዎች /የሥራ ሂደት አስተባባሪዎች/ የሚሞላ

መግቢያ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ (ኢኮቴ) ልማት ኤጀንሲ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ተግባራትን በኢኮቴ ዙሪያ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከልም በያዝነው በጀት አመት የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አንዱ ነው፡፡ በመሆኑም በክልሉ የመንግስት ተቋማት ለህዝብ በሚሰጡት አገልግሎት ላይ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል ለማወቅ የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አስፈልጓል፤ ጥናቱን ለማካሄድ የሚያስችል መረጃ ለማሰባሰብ ደግሞ ይህንን መጠይቅ አዘጋጅቷል፡፡ እርስዎም ይህንን መጠይቅ በጥንቃቄ በመሙላት ለጥናቱ መሳካት የበኩልዎን አስተዋጽኦ ያበረክቱ ዘንድ እየጠየቅን ለሚያደርጉልን ትብብር በቅድሚያ እናመሰግናለን፡፡ የጥናት ቡድኑ

ክፍል 1. አጠቃላይ የግል ሁኔታ፣

ስለግል ሁኔታዎ ትክክለኛ መልስ የያዘውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፣

1.1 ጾታ፣ 1. ወንድ 2. ሴት

1.2 ዕድሜ፣ 1. ከ18–27 ዓመት 2. ከ28–37 ዓመት 3. ከ38–47 ዓመት 4. ከ47 ዓመት በላይ

1.3 የሥራ ቦታ፣ 1. በክልል 2. በከተማ አስተዳደር 3. በዞን 4. በወረዳ

1.4 ያለዎት ከፍተኛው የትም/ደረጃ፣ 1. ሰርተፊኬትና በታች 2. ዲኘሎማ

3. የመጀመሪያ ዲግሪ 4. 2ኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ

1.5 የሥራ ልምድ፣ 1. ከ5 ዓመት በታች 2. ከ5–10 ዓመት 3. ከ11–15 ዓመት 4. ከ15 ዓመት

በላይ

1.6 በመሠረታዊ ኮምፒውተር ወይም በተዛማጅ የኢኮቴ ዘርፍ ያገኙት የሥልጠና ማስረጃ፣

1. የለኝም 2. ሰርቲፊኬት 3. ዲኘሎማ 4. ከዚያ በላይ ካለ ቢገለጽ

1.7 የኢኮቴ አገልግሎቶችን የት ያገኛሉ? / ከአንድ በላይ መልስ ሊኖረው ይችላል/

1. በመኖሪያ ቤቴ 2. ኢንተርኔት ካፌ 3. በመንግስት ተቋም

4. አላገኝም 5. በሌላ ካለ ቢገለጽ

ክፍል 2. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዕውቀት፣

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ የኢኮቴ ዕውቀት ደረጃዎን የሚመጥነውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡ መግለጫ፣

ከፍተኛ /4/ ስለ ጉዳዩ በጣም ጥሩ ዕውቀት አለኝ፣ መካከለኛ /3/ ስለጉዳዩ በቂ ዕውቀት አለኝ፣ ዝቅተኛ /2/ ስለ ጉዳዩ ጥቂት እውቀት አለኝ፣ ምንም /1/ ስለጉዳዩ ምንም እውቀት የለኝም፣ ወይም ጉዳዩን ፈጽሞ አላውቀውም፣

Page 73: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

2

ተ.ቁ ያለዎት የኢኮቴ ዕውቀት ከፍተ

ኛ መካከለ

ኛ ዝቅተኛ

ምንም

2.1 እንደ ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word / ያሉ ወርድ ኘሮሰሲንግ ዕውቀት፣

4 3 2 1

2.2 እንደ ኤክሴል / MS Excel / ያሉ ስኘሪድ ሽት ዕውቀት

4 3 2 1

2.3 እንደ ተደራሽነት / MS Access / ያሉ ዳታ ቤዞች ዕውቀት

4 3 2 1

2.4 እንደ ፓወርፖይንት ያሉ ፕረዘንቴሽን ሶፍትዌር በመጠቀም ስላይድ አዘገጃጀት ዕውቀት

4 3 2 1

2.5 በኢ-ሜል መልዕክት/መረጃ መላላክ ዕውቀት፣ 4 3 2 1 2.6 እንደ ጎግል፤ያሁ፤አስክ፤ኤምኤስኤን ወዘተ. ያሉ

የመረጃ መበርበሪያ መሣሪያዎች / Search engine / ዕውቀት

4 3 2 1

2.7 በሲዲ የተቀመጡ እንደ ኢንካርታ ኢንሳይክሎፒዲያ፣ ኤሌክትሮኒክ መጻህፍቶች / e- book / ወዘተ. ዕውቀት

4 3 2 1

2.8 የተለሙ አኘሊኬሽን ሶፍትዌሮችን የመጠቀም ዕውቀት

4 3 2 1

2.9 አይፒ ሜሴንጀር፤ ሜሴጅ ፖፕአፕ፤ኔትሚቲንግ ወዘተ. ዕውቀት

4 3 2 1

2.10 የLAN ዝርጋታ መሰረታዊ እውቀት 4 3 2 1 2.11 የኔትወርክ አስተዳደር እውቀት 4 3 2 1 2.12 ሶፍትዌር እና ዳታ ቤዞች ማልማት ዕውቀት 4 3 2 1 2.13 የኢኮቴ ዕቃዎች ሃርድዌርና ሶፍትዌር ጥገና

እና trouble shooting ዕውቀት 4 3 2 1

2.14 ድረ ገጽ ማልማትና ማሻሻል ዕውቀት 4 3 2 1 2.15 አዳዲስ የሚመጡ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች (እንደ

window 7, vista,…) ዕውቀት 4 3 2 1

2.16 የአድቫንስድ ኮምፒውተር ቋንቋ (C#, VB.Net, Java, SQL…) እውቀት

4 3 2 1

በሁለተኛና መሰናዶ ት/ቤቶች የኢኮቴ መምህራን ብቻ በተጨማሪ የሚሞላ 2.17 በኢኮቴ በመታገዝ ቤተ ሙከራን የሚተካ

ሲሙሌሽን የመጠቀም እውቀት 4 3 2 1

ክፍል 3፣ የዕለት ከዕለት ሥራዎ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የታገዘ ስለመሆኑ እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ የእለት ከእለት ስራዎ ከቴክኖሎጅው ጋር ያለውን ቁርኝት የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፡- ሁልጊዜ /4/ ስራየን በየዕለቱ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣ በተደጋጋሚ /3/ ስራዬን አብዛኛውን ጊዜ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣ አልፎ አልፎ /2/ ስራዬን አልፎ አልፎ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣ በጭራሽ /1/ በፍጹም ስራየን ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውኘ አላውቅም፣

Page 74: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

3

ተ.ቁ

የኢኮቴ አጠቃቀም ሁልጊዜ

በተደጋጋሚ

አልፎ አልፎ

በጭራሽ

3.1 እንደ ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word / ያሉ ወርድ ኘሮሰሲንግ በመጠቀም ደብዳቤ/ዶኩመንት ማዘጋጀት

4 3 2 1

3.2 እንደ ኤክሴል / MS Excel / ያሉ ስኘሪድ ሽት በመታገዝ እንደ ፔሮል፣ሰንጠረዥ፣ቻርት ወዘተ. ማዘጋጀት

4 3 2 1

3.3 እንደ ተደራሽነት / MS Access / ያሉ ዳታ ቤዞች በመጠቀም መረጃ መያዝ ማደራጀትና መተንትን

4 3 2 1

3.4 እንደ ፓወርፖይንት ያሉ ፕረዘንቴሽን ሶፍትዌር በመጠቀም ስላይድ አዘገጃጀት ዕውቀት

4 3 2 1

3.5 በኢ-ሜል መልዕክት/መረጃ መላላክ፣ 4 3 2 1 3.6 እንደ ጎግል፤ያሁ፤አስክ፤ኤምኤስኤን ወዘተ

ያሉ የመረጃ መበርበሪያ መሣሪያዎችን / Search engine / በመጠቀም መረጃ ማግኘት

4 3 2 1

3.7 በሲዲ የተቀመጡ እንደ ኢንካርታ ኢንሳይክሎፒዲያ፣ ኤሌክትሮኒክ መጻህፍቶች / e- book / ወዘተ. በመጠቀም መረጃ ማግኘት፣

4 3 2 1

3.8 LAN ዝርጋታን በመጠቀም ሀብትን መጋራት/ ለምሳሌ ፕሪንተር…/

4 3 2 1

3.9 የለሙ አኘሊኬሽን ሶፍትዌሮችን በመጠቀም መረጃ መያዝ፣ ማደራጀትና መተንትን

4 3 2 1

3.10 አይ ፒ ሜሴንጀር፤ ሜሴጅ ፖፕአፕ፤ኔትሚቲነግ ወዘተ. በመጠቀም መረጃ መለዋወጥ፤የመስመር ላይ ድጋፍ ማድረግ ወይም መቀበል

4 3 2 1

በሁለተኛና መሰናዶ ት/ቤቶች የኢኮቴ መምህራን ብቻ በተጨማሪ የሚሞላ 3.11 በኢኮቴ በመታገዝ ቤተ ሙከራን የሚተካ

ሲሙሌሽን ተጠቅሞ ማስተማር 4 3 2 1

Page 75: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

4

ክፍል 4. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መሣሪያዎች አቅርቦት ሁኔታ

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ በመስሪያ ቤትዎ ያለውን የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መሳሪያዎችን አቅርቦት ሁኔታ የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፡- ከፍተኛ /4/ ከሚፈለገው /ከስታንዳርዱ / በላይ የሆነ አቅርቦት፣ መካከለኛ /3/ ስታንዳርዱን የጠበቀና በቂ የሆነ አቅርቦት፣ ዝቅተኛ /2/ በመጠኑም መሻሻል የሚገባው /ስታንዳርዱን / ያልጠበቀ አቅርቦት፣ ምንም /1/ ምንም አይነት አቅርቦት የለም፣

ተ.ቁ የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ ምንም

4.1 ኮምፒውተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሣሪያዎች 4 3 2 1 4.2 የዲያላኘ / dial up / ፣ ብሮድባንድ፣

CDMA ወዘተ. የኢንተርኔት አገልግሎት 4 3 2 1

4.3 የወረዳ ኔት ወይም የስኩል ኔት አገልግሎት 4 3 2 1 4.4 የLAN መሠረተ ልማት ዝርጋታ 4 3 2 1 4.5 የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች 4 3 2 1 4.6 የለማ ድረገጽ 4 3 2 1 4.7 የባለቤትነት መብት ያላቸው አንቲቫይረሶች 4 3 2 1 ክፍል 5፣ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ በመስሪያ ቤትዎ የአገልግሎት ሰጭ ሰራተኞችንና የቴክኖሎጅውን ቁርኝት የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፣ ሁሉም /4/ የተቋሙ ሰራተኞች በሙሉ አብዛኛው /3/ አብዛኞቹ የተቋሙ ሰራተኞች ጥቂት /2/ ጥቂት የተቋሙ ሰራተኞች ምንም /1/ አንድም የተቋሙ ሰራተኛ የለም

Page 76: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

5

ተ.ቁ የኢኮቴ ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን ሁሉም አብዛኛው ጥቂት ምንም 5.1 ኮምፒውተርና ተዛማጅ የኢኮቴ መሣሪያዎች

ተጠቃሚ የሠራተኛ መጠን፣ 4 3 2 1

5.2 ኢንተርኔት ፣ወረዳኔት ወይም ስኩልኔት ተጠቃሚ ሠራተኛ መጠን

4 3 2 1

5.3 በLAN መሠረተ ልማት የታገዘ አገልግሎት ሰጭ ሠራተኛ መጠን፣

4 3 2 1

5.4 የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች ተጠቃሚ ሠራተኛ ብዛት፣

4 3 2 1

5.5 የተቋሙን ድረ ገጽ ተጠቃሚ ሠራተኛ ብዛት፣

4 3 2 1

5.6 የቪዲዮ ኮንፈረንስ ተጠቃሚ ሰራተኛ መጠን 4 3 2 1

ክፍል 6. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በአገልግሎት አሰጣጥዎ ላይ ያለው ተፅዕኖ እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ በአገልግሎት አሰጣጥዎ ሂደት የቴክኖሎጅው ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፣ ከታች በሰንጠረዡ በዝርዝር በተገለጸው ሃሳብ- በጣም እስማማለሁ /5/ እስማማለሁ /4/ አላወኩም /3/ አልስማማም /2/ በጣም አልስማማም /1/

ተ.ቁ

በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢኮቴ ተጽዕኖ በጣም

እስማማለሁ

እስማማለሁ

አላወኩም

አልስማማም

በጣም አልስማማም

6.1 ኮምፒውተር /በአጠቃላይ የኢኮቴ ዕቃዎች/ ሥራየን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድተውኛል፤

5 4 3 2 1

6.2 ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word/ በመጠቀም ደብዳቤ ፣ዶክመንት ወ.ዘ.ተ በቀላሉ ለማዘጋጀት ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

6.3 እንደ ኤክስኤል ያሉ በመጠቀሜ ፔሮል፣ ሰንጠረዥ፣ቻርት፣ ማርክ ሊስት፣ሮስተር… የመሳሰሉትን በፍጥነት ለማዘጋጀትና መረጃን ለማደራጀት ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

6.4 ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ አግዞኛል፤

5 4 3 2 1

6.5 የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን፣ ጊዜንና ወጭን ቆጥቧል፣

5 4 3 2 1

6.6 አይ.ፒ ሜሴንጀር ፣ ሜሴጅ ፖኘ አኘ፣ ኔት ሚቲንግ የመሳሰሉት ሶፍትዌሮችን መጠቀም ስራን አቃሏል፤ ወጪን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

6.7 ወረዳኔት ወይም ስኩልኔት የተለያዩ አገልግሎቶች 5 4 3 2 1

Page 77: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

6

ተ.ቁ

በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢኮቴ ተጽዕኖ

በጣም

እስማማለሁ

እስማማለሁ

አላወኩም

አልስማማም

በጣም አልስማማም

በየአካባቢው በስፋት እንዲዳረሱ በማድረጉ ገንዘብን ፣ጊዜንና ጉልበትን ቆጥቧል፤

6.8 ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

6.9 ኢኮቴን በመጠቀም የመስመር ላይ ድጋፍ ማድረግ /ማግኘት/ አስችሎኛል፤

5 4 3 2 1

6.10 ኢኮቴ የሥራ ተነሣሽነቴን ጨምሮልኛል፤ 5 4 3 2 1 6.11 በገንዘብ ልገዛው የማልችለውን ማቴሪያል ኢኮቴ

በነጻ እንዳገኝ አስችሎኛል፤ 5 4 3 2 1

6.12 ኢኮቴ የአሠራር ዘዴን በማሻሻሉ ውጣ ውረድን አሳጥሯል፤

5 4 3 2 1

6.13 ኢኮቴን መጠቀም የሰራተኛውን ብሎም የተቋሙን እቅድ አፈጻጸም አሻሽሏል፤

5 4 3 2 1

6.14 ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ ልውውጥ በማከናወን ጊዜን፣ጉልበትን፣ቦታንና ወጭን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

6.15 ከክልል እስከ ወረዳ መዋቅር ያላቸው ተቋማት ኦቶሜት መደረግ አለባቸው፤

5 4 3 2 1

6.16 የሁሉም ተቋማት መረጃ አያያዝና ሪፖርት ልውውጥ በወረዳ ኔት፣ ስኩል ኔት፣ ዌብቤዝድ ዳታቤዞች ወዘተ. መታገዝ አለባቸው፤

5 4 3 2 1

Page 78: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

7

ክፍል 7. አጠቃላይ አስተያየት 7.1 በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መታገዝ አለባቸው የሚሏቸውን አገልግሎቶች

ቢጠቁሙን 7.2 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በተቋምዎ ያስገኛቸውን ዋና ዋና ጥቅሞች ቢዘረዝሩልን

7.3 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን ለመጠቀም ያጋጠሙ ችግሮች የሚሏቸውን ቢጠቁሙን

7.4 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዉጤታማና ቀልጣፋ የሆነ የመንግስት አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችል ወደፊት ምን መደረግ አለበት ይላሉ?

______________________________________________________________________________________________________________________________________________

በድጋሜ እናመሰግናለን፡፡

Page 79: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

1

አባሪ 4

መጠይቅ 2፣ በተቋሙ ደንበኞች የሚሞላ

መግቢያ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ (ኢኮቴ) ልማት ኤጀንሲ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ተግባራትን በኢኮቴ ዙሪያ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከልም በያዝነው በጀት አመት የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አንዱ ነው፡፡ በመሆኑም በክልሉ የመንግስት ተቋማት ለህዝብ በሚሰጡት አገልግሎት ላይ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል ለማወቅ የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አስፈልጓል፤ ጥናቱን ለማካሄድ የሚያስችል መረጃ ለማሰባሰብ ደግሞ ይህንን መጠይቅ አዘጋጅቷል፡፡ እርስዎም ይህንን መጠይቅ በጥንቃቄ በመሙላት ለጥናቱ መሳካት የበኩልዎን አስተዋጽኦ ያበረክቱ ዘንድ እየጠየቅን ለሚያደርጉልን ትብብር በቅድሚያ እናመሰግናለን፡፡ የጥናት ቡድኑ ክፍል 1. አጠቃላይ የግል ሁኔታ፣ ስለግል ሁኔታዎ ትክክለኛ መልስ የያዘውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፣

1.1 ጾታ፣ 1. ወንድ 2. ሴት

1.2 ዕድሜ፣ 1. ከ18 –27 ዓመት 2. ከ28–37 ዓመት 3. ከ38–47 ዓመት 4.ከ47 ዓመት

በላይ

1.3 የመኖሪያ ቦታ፣ 1. በክልል 2. በከተማ አስተዳደር 3. በዞን 4. በወረዳ

1.4 ያለዎት ከፍተኛው የትምህርት ደረጃ፣ 1. ሰርተፊኬትና በታች 2. ዲኘሎማ

3. የመጀመሪያ ዲግሪ 4. 2ኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ

1.5 በመሠረታዊ ኮምፒውተር ወይም በተዛማጅ የኢኮቴ ዘርፍ ያገኙት የሥልጠና ማስረጃ፣

1.የለኝም 2. ሰርተፊኬት 3. ዲኘሎማ 4. ከዚያ በላይ ካለ ቢገለጽ

ክፍል 2. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለው ተፅዕኖ

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት የቴክኖሎጅው ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፣ ከታች በሰንጠረዡ በዝርዝር በተገለጸው ሃሳብ-

በጣም እስማማለሁ /5/ እስማማለሁ /4/ አላወኩም /3/ አልስማማም /2/ በጣም አልስማማም /1/

Page 80: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

2

ተ.ቁ

የኢኮቴ ተጽዕኖ በአገልግሎት አሰጣጥ

ላይ

በጣም እስማማለ

እስማማለሁ

አላወኩም

አልስማማም

በጣም አልስማማም

2.1 የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመታገዙ ቀልጣፋና ውጤታማ ሆኗል፣

5 4 3 2 1

2.2 የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመታገዙ አገልግሎት አሰጣጡ አርክቶኛል፣

5 4 3 2 1

2.3 በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የታገዘ አገልግሎት በአካባቢዬ በማግኘቴ ጊዜ፣ጉልበትንና ወጪን ቆጥቦልኛል፣

5 4 3 2 1

2.4 የመ/ቤቱ አገልግሎት በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመታገዙ አገልግሎት አሰጣጡ ግልጽና ፍትሃዊ ሆኗል፡፡

5 4 3 2 1

2.5 በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ምክንያት የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት ጨምሯል፤

5 4 3 2 1

2.6 በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ምክንያት የመስሪያ ቤቱ መረጃ አያያዝና አደረጃጀት ተሻሽሏል፡፡

5 4 3 2 1

ክፍል 3. አጠቃላይ አስተያየት 3.1 በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መታገዝ አለባቸው የሚሏቸውን አገልግሎቶች

ቢጠቁሙን

3.2 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ያስገኛቸውን ዋና ዋና ጥቅሞች ቢዘረዝሩልን 3.3 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን ለመጠቀም ያጋጠሙ ችግሮች የሚሏቸውን ቢጠቁሙን

3.4 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዉጤታማና ቀልጣፋ የሆነ የመንግስት አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችል ወደፊት ምን መደረግ አለበት ይላሉ? ______________________________________________________________________________________________________________________________________________

በድጋሜ እናመሰግናለን፡፡

Page 81: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

1

አባሪ 5 መጠይቅ 3. በተቋሙ ሰራተኞች የሚሞላ

መግቢያ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ (ኢኮቴ) ልማት

ኤጀንሲ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ተግባራትን በኢኮቴ ዙሪያ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከልም በያዝነው በጀት አመት የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አንዱ

ነው፡፡ በመሆኑም በክልሉ የመንግስት ተቋማት ለህዝብ በሚሰጡት አገልግሎት ላይ

የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል ለማወቅ የዳሰሳ ጥናት

ማካሄድ አስፈልጓል፤ ጥናቱን ለማካሄድ የሚያስችል መረጃ ለማሰባሰብ ደግሞ ይህንን መጠይቅ

አዘጋጅቷል፡፡ እርስዎም ይህንን መጠይቅ በጥንቃቄ በመሙላት ለጥናቱ መሳካት የበኩልዎን

አስተዋጽኦ ያበረክቱ ዘንድ እየጠየቅን ለሚያደርጉልን ትብብር በቅድሚያ እናመሰግናለን፡፡

የጥናት ቡድኑ

ክፍል 1. አጠቃላይ የግል ሁኔታ፣

ስለግል ሁኔታዎ ትክክለኛ መልስ የያዘውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፣

1.6 ጾታ፣ 1. ወንድ 2. ሴት

1.7 ዕድሜ፣ 1. ከ18–27 ዓመት 2. ከ28–37 ዓመት 3. ከ38–47 ዓመት 4. ከ47 ዓመት በላይ

1.8 የሥራ ቦታ፣ 1. በክልል 2. በከተማ አስተዳደር 3. በዞን 4. በወረዳ

1.9 ያለዎት ከፍተኛው የትም/ደረጃ፣ 1. ሰርተፊኬትና በታች 2. ዲኘሎማ

3. የመጀመሪያ ዲግሪ 4. 2ኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ

1.10 የሥራ ልምድ፣ 1. ከ5 ዓመት በታች 2. ከ5–10 ዓመት 3. ከ11–15 ዓመት 4. ከ15 ዓመት

በላይ

1.6 በመሠረታዊ ኮምፒውተር ወይም በተዛማጅ የኢኮቴ ዘርፍ ያገኙት የሥልጠና ማስረጃ፣

2. የለኝም 2. ሰርተፊኬት 3. ዲኘሎማ 4. ከዚያ በላይ ካለ ቢገለጽ

1.8 የኢኮቴ አገልግሎቶችን የት ያገኛሉ? / ከአንድ በላይ መልስ ሊኖረው ይችላል/

1. በመኖሪያ ቤቴ 2. ኢንተርኔት ካፌ 3. ከመንግስት ተቋም

4. አላገኝም 5. በሌላ ካለ ይገለጽ

Page 82: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

2

ክፍል 2. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዕውቀት፣ እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ የኢኮቴ ተዛማጅ ዕውቀትና ልምድ ደረጃዎን የሚመጥነውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡ መግለጫ፣

ከፍተኛ /4/ ስለ ጉዳዩ በጣም ጥሩ ዕውቀት አለኝ፣ መካከለኛ /3/ ስለጉዳዩ በቂ ዕውቀት አለኝ፣ ዝቅተኛ /2/ ስለ ጉዳዩ ጥቂት እውቀት አለኝ፣ ምንም /1/ ስለጉዳዩ ምንም እውቀት የለኝም፣ ወይም ጉዳዩን ፈጽሞ አላውቀውም፣

ተ.ቁ

ያለዎት የኢኮቴ እውቀት ከፍተኛ

መካከለኛ

ዝቅተኛ

ምንም

2.1 እንደ ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word / ያሉ

ወርድ ኘሮሰሲንግ ዕውቀት፣ 4 3 2 1

2.2 እንደ ኤክሴል / MS Excel / ያሉ ስኘሪድ ሽት ዕውቀት

4 3 2 1

2.3 እንደ ተደራሽነት / MS Access / ያሉ ዳታ ቤዞች ዕውቀት

4 3 2 1

2.4 እንደ ፓወርፖይንት ያሉ ፕረዘንቴሽን ሶፍትዌር በመጠቀም ስላይድ አዘገጃጀት ዕውቀት

4 3 2 1

2.5 በኢ-ሜል መልዕክት/መረጃ መላላክ ዕውቀት ፣ 4 3 2 1 2.6 እንደ ጎግል፤ያሁ፤አስክ፤ኤምኤስኤን ወዘተ ያሉ

የመረጃ መበርበሪያ መሣሪያዎች / Search engine / ዕውቀት

4 3 2 1

2.7 በሲዲ የተቀመጡ እንደ ኢንካርታ ኢንሳይክሎፒዲያ፣ ኤሌክትሮኒክ መጻህፍቶች / e- book / ወዘተ. ዕውቀት

4 3 2 1

2.8 የተለሙ አኘሊኬሽን ሶፍትዌሮች መጠቀም ዕውቀት

4 3 2 1

2.9 አይፒ ሜሴንጀር፤ ሜሴጅ ፖፕአፕ፤ኔትሚቲንግ ወዘተ. ዕውቀት

4 3 2 1

ክፍል 3፣ የዕለት ከዕለት ሥራዎ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የታገዘ ስለመሆኑ እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ የእለት ከእለት ስራዎና ቴክኖሎጅው ያላቸውን ቁርኝት የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡ መግለጫ፡-

ሁልጊዜ /4 ስራየን በየዕለቱ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣

በተደጋጋሚ /3/ ስራዬን አብዛኛውን ጊዜ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣

አልፎ አልፎ /2/ ስራዬን አልፎ አልፎ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣

በጭራሽ /1/ በፍጹም ስራየን ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውኘ አላውቅም፣

Page 83: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

3

ተ.ቁ የኢኮቴ አጠቃቀም

በጣም በተደጋጋሚ

በተደጋጋሚ

አልፎ አልፎ

በጭራሽ

3.1 እንደ ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word / ያሉ ወርድ ኘሮሰሲንግ በመጠቀም ደብዳቤ/ዶኩመንት ማዘጋጀት

4 3 2 1

3.2 እንደ ኤክሴል / MS Excel / ያሉ ስኘሪድ ሽት በመታገዝ እንደ ፔሮል፣ሰንጠረዥ፣ቻርት ወዘተ. ማዘጋጀት

4 3 2 1

3.3 እንደ ተደራሽነት / MS Access / ያሉ ዳታ ቤዞች በመጠቀም መረጃ መያዝ ማደራጀትና መተንትን

4 3 2 1

3.4 እንደ ፓወርፖይንት ያሉ ፕረዘንቴሽን ሶፍትዌር በመጠቀም ሪፖርት ማዘጋጀት

4 3 2 1

3.5 በኢ-ሜል መልዕክት/መረጃ መላላክ፣ 4 3 2 1 3.6 እንደ ጎግል፤ያሁ፤አስክ፤ኤምኤስኤን ወዘተ

ያሉ የመረጃ መበርበሪያ መሣሪያዎችን / Search engine / በመጠቀም መረጃ ማግኘት

4 3 2 1

3.7 በሲዲ የተቀመጡ እንደ ኢንካርታ ኢንሳይክሎፒዲያ፣ ኤሌክትሮኒክ መጻህፍቶች / e- book / ወዘተ. በመጠቀም መረጃ ማግኘት፣

4 3 2 1

3.8 LAN ዝርጋታን በመጠቀም ሀብትን መጋራት / ለምሳሌ ፕሪንተር…/

4 3 2 1

3.9 የለሙ አኘሊኬሽን ሶፍትዌሮችን በመጠቀም መረጃ መያዝ፣ ማደራጀትና መተንትን

4 3 2 1

3.10 አይፒ ሜሴንጀር፣ ሜሴጅ ፖፕአፕ፣ኔትሚቲንግ ወዘተ. በመጠቀም መረጃ መለዋወጥ፤የመስመር ላይ ድጋፍ ማድረግ ወይም መቀበል

4 3 2 1

ክፍል 4. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በአገልግሎት አሰጣጥዎ ላይ ያለው ተፅዕኖ

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ በአገልግሎት አሰጣጥዎ ሂደት የቴክኖሎጅው ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፣ ከታች በሰንጠረዡ በዝርዝር በተገለጸው ሃሳብ- በጣም እስማማለሁ /5/ እስማማለሁ /4/ አላወኩም /3/ አልስማማም /2/ በጣም አልስማማም /1/

Page 84: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

4

ተ.ቁ

በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢኮቴ ተጽዕኖ

በጣም

እስማማለሁ

እስማማለሁ

አላወኩም

አልስማማም

በጣም አልስማማም

4.1 ኮምፒውተር /በአጠቃላይ የኢኮቴ ዕቃዎች/ ሥራየን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድተውኛል፤

5 4 3 2 1

4.2 ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word/ በመጠቀም ደብዳቤ ፣ዶክመንት ወ.ዘ.ተ በቀላሉ ለማዘጋጀት ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

4.3 እንደ ኤክስኤል ያሉ በመጠቀሜ ፔሮል፣ ሰንጠረዥ፣ቻርት የመሳሰሉትን በፍጥነት ለማዘጋጀትና መረጃን ለማደራጀት ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

4.4 ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ አግዞኛል፤

5 4 3 2 1

4.5 የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን፣ ጊዜንና ወጭን ቆጥቧል፣

5 4 3 2 1

4.6 አይ.ፒ ሜሴንጀር ፣ ሜሴጅ ፖኘ አኘ፣ ኔት ሚቲንግ የመሳሰሉት ሶፍትዌሮችን መጠቀም ስራን አቃሏል፤ ወጪን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

4.7 ወረዳኔት የተለያዩ አገልግሎቶች በየአካባቢው በስፋት እንዲዳረሱ በማድረጉ ገንዘብን ፣ጊዜንና ጉልበትን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

4.8 ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

4.9 ኢኮቴን በመጠቀም የመስመር ላይ ድጋፍ ማድረግ /ማግኘት/ አስችሎኛል፤

5 4 3 2 1

4.10 ኢኮቴ የሥራ ተነሣሽነቴን ጨምሮልኛል፤ 5 4 3 2 1 4.11 በገንዘብ ልገዛው የማልችለውን ማቴሪያል ኢኮቴ

በነጻ እንዳገኝ አስችሎኛል፤ 5 4 3 2 1

4.12 ኢኮቴ የአሠራር ዘዴን በማሻሻሉ ውጣ ውረድን አሳጥሯል፤

5 4 3 2 1

4.13 ኢኮቴን መጠቀም የሰራተኛውን ብሎም የተቋሙን እቅድ አፈጻጸም አሻሽሏል፤

5 4 3 2 1

4.14 ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ ልውውጥ በማከናወን ጊዜን፣ጉልበትን፣ቦታንና ወጭን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

4.15 ከክልል እስከ ወረዳ መዋቅር ያላቸው ሴክተሮች ኦቶሜት መደረግ አለባቸው፤

5 4 3 2 1

4.16 የሁሉም ሴክተሮች መረጃ አያያዝና ሪፖርት ልውውጥ በወረዳ ኔት፣ ዌብቤዝድ ዳታቤዞች ወዘተ. መታገዝ አለባቸው፤

5 4 3 2 1

Page 85: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

5

ክፍል 5. አጠቃላይ አስተያየት 5.1 በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መታገዝ አለባቸው የሚሏቸውን አገልግሎቶች

ቢጠቁሙን

5.2 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በተቋምዎ ያስገኛቸውን ዋና ዋና ጥቅሞች

ቢዘረዝሩልን

5.3 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን ለመጠቀም ያጋጠሙ ችግሮች የሚሏቸውን

ቢጠቁሙን

5.4 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዉጤታማና ቀልጣፋ የሆነ የመንግስት አገልግሎት

ለመስጠት እንዲያስችል ወደፊት ምን መደረግ አለበት ይላሉ? ______________________________________________________________________________________________________________________________________________

በድጋሜ እናመሰግናለን፡፡

Page 86: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

1

አባሪ 6

መጠይቅ 4. በተቋሙ የበላይ ሃላፊዎች የሚሞላ

መግቢያ

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ (ኢኮቴ) ልማት

ኤጀንሲ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ተግባራትን በኢኮቴ ዙሪያ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከልም በያዝነው በጀት አመት የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አንዱ

ነው፡፡ በመሆኑም በክልሉ የመንግስት ተቋማት ለህዝብ በሚሰጡት አገልግሎት ላይ

የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል ለማወቅ የዳሰሳ ጥናት

ማካሄድ አስፈልጓል፤ ጥናቱን ለማካሄድ የሚያስችል መረጃ ለማሰባሰብ ደግሞ ይህንን መጠይቅ

አዘጋጅቷል፡፡ እርስዎም ይህንን መጠይቅ በጥንቃቄ በመሙላት ለጥናቱ መሳካት የበኩልዎን

አስተዋጽኦ ያበረክቱ ዘንድ እየጠየቅን ለሚያደርጉልን ትብብር በቅድሚያ እናመሰግናለን፡፡

የጥናት ቡድኑ

ክፍል 1. አጠቃላይ የግል ሁኔታ፣ ስለግል ሁኔታዎ ትክክለኛ መልስ የያዘውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፣

1.11 ጾታ፣ 1. ወንድ 2. ሴት

1.12 ዕድሜ፣ 1. ከ18–27 ዓመት 2. ከ28–37 ዓመት 3. ከ38–47 ዓመት 4. ከ47 ዓመት

በላይ

1.13 የሥራ ቦታ፣ 1. በክልል 2. በከተማ አስተዳደር 3. በዞን 4. በወረዳ

1.14 ያለዎት ከፍተኛው የትም/ደረጃ፣ 1. ሰርተፊኬትና በታች 2. ዲኘሎማ

3. የመጀመሪያ ዲግሪ 4. 2ኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ

1.15 የሥራ ልምድ፣ 1. ከ5 ዓመት በታች 2. ከ5–10 ዓመት 3. ከ11–15 ዓመት 4. ከ15

ዓመት በላይ

1.6 በመሠረታዊ ኮምፒውተር ወይም በተዛማጅ የኢኮቴ ዘርፍ ያገኙት የሥልጠና ማስረጃ፣

3. የለኝም 2. ሰርተፊኬት 3. ዲኘሎማ 4. ከዚያ በላይ ካለ ቢገለጽ

1.9 የኢኮቴ አገልግሎቶችን የት ያገኛሉ? / ከአንድ በላይ መልስ ሊኖረው ይችላል/

1. በመኖሪያ ቤቴ 2. ከኢንተርኔት ካፌ 3. ከመንግስት ተቋም

4. አላገኝም 5. በሌላ ካለ ይገለጽ

Page 87: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

2

ክፍል 2. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዕውቀት፣

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ የኢኮቴ ተዛማጅ ዕውቀት ደረጃዎን የሚመጥነውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡ መግለጫ፣

ከፍተኛ /4/ ስለ ጉዳዩ በጣም ጥሩ ዕውቀት አለኝ፣ መካከለኛ /3/ ስለጉዳዩ በቂ ዕውቀት አለኝ፣ ዝቅተኛ /2/ ስለ ጉዳዩ ጥቂት እውቀት አለኝ፣ ምንም /1/ ስለጉዳዩ ምንም እውቀት የለኝም፣ ወይም ጉዳዩን ፈጽሞ አላውቀውም፣

ተ.ቁ

ያለዎት የኢኮቴ እውቀት ከፍተኛ መካከለኛ

ዝቅተኛ

ምንም

2.1 እንደ ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word / ያሉ ወርድ ኘሮሰሲንግ ዕውቀት፣

4 3 2 1

2.2 እንደ ኤክሴል / MS Excel / ያሉ ስኘሪድ ሽት ዕውቀት

4 3 2 1

2.3 እንደ ተደራሽነት / MS Access / ያሉ ዳታ ቤዞች ዕውቀት

4 3 2 1

2.4 እንደ ፓወርፖይንት ያሉ ፕረዘንቴሽን ሶፍትዌር በመጠቀም ስላይድ አዘገጃጀት ዕውቀት

4 3 2 1

2.5 በኢ-ሜል መልዕክት/መረጃ መላላክ ዕውቀት፣ 4 3 2 1 2.6 እንደ ጎግል፤ያሁ፤አስክ፤ኤምኤስኤን ወዘተ ያሉ

የመረጃ መበርበሪያ መሣሪያዎችን / Search engine / ዕውቀት

4 3 2 1

2.7 በሲዲ የተቀመጡ እንደ ኢንካርታ ኢንሳይክሎፒዲያ፣ ኤሌክትሮኒክ መጻህፍቶች / e- book / ወዘተ ዕውቀት

4 3 2 1

2.8 የተለሙ አኘሊኬሽን ሶፍትዌሮችን መጠቀም ዕውቀት 4 3 2 1 2.9 አይፒ ሜሴንጀር፤ ሜሴጅ ፖፕአፕ፤ኔትሚቲንግ

ወዘተ. ዕውቀት 4 3 2 1

ክፍል 3፣ የዕለት ከዕለት ሥራዎ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የታገዘ ስለመሆኑ እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ የእለት ከእለት ስራዎና ቴክኖሎጅው ያላቸውን ቁርኝት የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡ መግለጫ፡-

በጣም በተደጋጋሚ /5/ ስራየን በየዕለቱ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣ በተደጋጋሚ /4/ ስራዬን አብዛኛውን ጊዜ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ

አከናውናለሁ፣ አንዳንድ ጊዜ /3/ ስራየን አንዳንድ ጊዜ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣ አልፎ አልፎ /2/ ስራዬን አልፎ አልፎ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውናለሁ፣ በጭራሽ /1/ በፍጹም ስራየን ቴክኖሎጅውን ተጠቅሜ አከናውኘ አላውቅም፣

Page 88: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

3

ተ.ቁ የኢኮቴ አጠቃቀም በጣም በተደጋጋሚ

በተደጋጋሚ

አንዳንድ ጊዜ

አልፎ አልፎ

በጭራሽ

3.1 እንደ ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word / ያሉ ወርድ ኘሮሰሲንግ በመጠቀም ደብዳቤ/ዶኩመንት ማዘጋጀት

5 4 3 2 1

3.2 እንደ ኤክሴል / MS Excel / ያሉ ስኘሪድ ሽት በመታገዝ እንደ ፔሮል፣ሰንጠረዥ፣ቻርት ወዘተ. ማዘጋጀት

5 4 3 2 1

3.3 እንደ ተደራሽነት / MS Access / ያሉ ዳታ ቤዞች በመጠቀም መረጃ መያዝ ማደራጀትና መተንትን

5 4 3 2 1

3.4 እንደ ፓወርፖይንት ያሉ ፕረዘንቴሽን ሶፍትዌር በመጠቀም ስላይድ አዘጋጅቶ ጽሁፍ/ሪፖርት ማቅረብ

5 4 3 2 1

3.5 በኢ-ሜል መልዕክት/መረጃ መላላክ፣ 5 4 3 2 1 3.6 እንደ ጎግል፤ያሁ፤አስክ፤ኤምኤስኤን ወዘተ

ያሉ የመረጃ መበርበሪያ መሣሪያዎችን / Search engine / በመጠቀም መረጃ ማግኘት

5 4 3 2 1

3.7 በሲዲ የተቀመጡ እንደ ኢንካርታ ኢንሳይክሎፒዲያ፣ ኤሌክትሮኒክ መጻህፍቶች / e- book / ወዘተ በመጠቀም መረጃ ማግኘት፣

5 4 3 2 1

3.8 LAN ዝርጋታን በመጠቀም ሀብትን መጋራት /ለምሳሌ ፕሪንተር…/

5 4 3 2 1

3.9 የለሙ አኘሊኬሽን ሶፍትዌሮችን በመጠቀም መረጃ መያዝ፣ ማደራጀትና መተንትን

5 4 3 2 1

3.10 አይ ፒ ሜሴንጀር፤ ሜሴጅ ፖፕአፕ፤ኔትሚቲንግ ወዘተ. በመጠቀም መረጃ መለዋወጥ፤የመስመር ላይ ድጋፍ ማድረግ ወይም መቀበል

5 4 3 2 1

ክፍል 4. ለኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የተሰጠው ትኩረት

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ በመስሪያ ቤትዎ ለኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ የሰጠውን ትኩረት የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፡- ከታች በሰንጠረዡ ኢኮቴን አስመልክቶ ለተጠቀሰው ጉዳይ የተሰጠው ትኩረት፡- ከፍተኛ /4/ መካከለኛ /3/ ዝቅተኛ /2/ ምንም /1/

Page 89: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

4

ተ.ቁ ለኢኮቴ የተሰጠው ትኩረት ከፍተኛ

መካከለኛ

ዝቅተኛ

ምንም

4.1 ለኢኮቴ የሚመደብ የበጀት ድርሻ 4 3 2 1 4.2 ኢኮቴን አስመልክቶ የተዘጋጀ አውደ ጥናት፣አጫጭር

ስልጠና ወዘተ. ብዛት 4 3 2 1

4.3 ለኢኮቴ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ምቹ የስራ ቦታ 4 3 2 1 4.4 ራሱን የቻለ የስልጠና ማዕከል መዘጋጀቱ 4 3 2 1 4.5 ራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል መዘጋጀቱ 4 3 2 1 4.6 የቪዲዮ ኮንፈረንስ አዳራሽ ራሱን ችሎ መኖሩና

በተገቢው ቁሳቁስ መደራጀቱ 4 3 2 1

4.7 በተቋሙ ውስጥ ኢኮቴን አስመልክቶ በባለሙያዎች / በሃላፊዎች የተደረገ ጥናትና ምርምር ብዛት

4 3 2 1

4.8 ራሱን የቻለ ሰርቨር ሩም መኖሩ 4 3 2 1 4.9 በኢኮቴ የሰለጠነ የሰው ሀይል ብዛት 4 3 2 1 ክፍል 5. የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በአገልግሎት አሰጣጥዎ ላይ ያለው ተፅዕኖ

እባክዎን መግለጫውን በትክክል በመገንዘብ በአገልግሎት አሰጣጥዎ ሂደት የቴክኖሎጅው ተጽዕኖ ምን እንደሚመስል የሚገልጸውን ቁጥር በማክበብ ይመልሱ፡፡

መግለጫ፣ ከታች በሰንጠረዡ በዝርዝር በተገለጸው ሃሳብ- በጣም እስማማለሁ /5/ እስማማለሁ /4/ አላወኩም /3/ አልስማማም /2/ በጣም አልስማማም /1/

ተ.ቁ

በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢኮቴ ተጽዕኖ

በጣም

እስማማለሁ

እስማማለሁ

አላወኩም

አልስማማም

በጣም አልስማማም

5.1 ኮምፒውተር /በአጠቃላይ የኢኮቴ ዕቃዎች/ ሥራየን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት ረድተውኛል፤

5 4 3 2 1

5.2 ማይክሮሶፍት ወርድ /MS Word/ በመጠቀም ደብዳቤ ፣ዶክመንት ወ.ዘ.ተ በቀላሉ ለማዘጋጀት ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

5.3 እንደ ኤክስኤል ያሉ በመጠቀሜ ፔሮል፣ ሰንጠረዥ፣ቻርት የመሳሰሉትን በፍጥነት ለማዘጋጀትና መረጃን ለማደራጀት ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

5.4 ኢንተርኔት መረጃን በቀላሉ ለማግኘትና ለመለዋወጥ አግዞኛል፤

5 4 3 2 1

5.5 የLAN ዝርጋታ መኖሩ ሀብትን፣ ጊዜንና ወጭን ቆጥቧል፣

5 4 3 2 1

Page 90: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

5

ተ.ቁ

በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢኮቴ ተጽዕኖ

በጣም

እስማማለሁ

እስማማለሁ

አላወኩም

አልስማማም

በጣም አልስማማም

5.6 አይ.ፒ ሜሴንጀር ፣ ሜሴጅ ፖኘ አኘ፣ ኔት ሚቲንግ የመሳሰሉት ሶፍትዌሮችን መጠቀም ስራን አቃሏል፤ ወጪን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

5.7 ወረዳኔት የተለያዩ አገልግሎቶች በየአካባቢው በስፋት እንዲዳረሱ በማድረጉ ገንዘብን ፣ጊዜንና ጉልበትን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

5.8 ኢኮቴ አስተማማኝ መረጃ በቀላሉና በፍጥነት ለመለዋወጥ ረድቶኛል፤

5 4 3 2 1

5.9 ኢኮቴን በመጠቀም የመስመር ላይ ድጋፍ ማድረግ /ማግኘት/ አስችሎኛል፤

5 4 3 2 1

5.10 ኢኮቴ የሥራ ተነሣሽነቴን ጨምሮልኛል፤ 5 4 3 2 1 5.11 በገንዘብ ልገዛው የማልችለውን ማቴሪያል ኢኮቴ

በነጻ እንዳገኝ አስችሎኛል፤ 5 4 3 2 1

5.12 ኢኮቴ የአሠራር ዘዴን በማሻሻሉ ውጣ ውረድን አሳጥሯል፤

5 4 3 2 1

5.13 ኢኮቴን መጠቀም የሰራተኛውን ብሎም የተቋሙን እቅድ አፈጻጸም አሻሽሏል፤

5 4 3 2 1

5.14 ኢኮቴን ተጠቅሞ ወረቀት አልባ የመረጃ ልውውጥ በማከናወን ጊዜን፣ጉልበትን፣ቦታንና ወጭን ቆጥቧል፤

5 4 3 2 1

5.15 ከክልል እስከ ወረዳ መዋቅር ያላቸው ሴክተሮች ኦቶሜት መደረግ አለባቸው፤

5 4 3 2 1

5.16 የሁሉም ሴክተሮች መረጃ አያያዝና ሪፖርት ልውውጥ በወረዳ ኔት፣ ዌብቤዝድ ዳታቤዞች ወዘተ. መታገዝ አለባቸው፤

5 4 3 2 1

Page 91: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

6

ክፍል 6. አጠቃላይ አስተያየት 6.1 በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ መታገዝ አለባቸው የሚሏቸውን አገልግሎቶች ቢጠቁሙን 6.2 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ በተቋምዎ ያስገኛቸውን ዋና ዋና ጥቅሞች ቢዘረዝሩልን 6.3 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅን ለመጠቀም ያጋጠሙ ችግሮች የሚሏቸውን ቢጠቁሙን 6.4 ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ዉጤታማና ቀልጣፋ የሆነ የመንግስት አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችል ወደፊት ምን መደረግ አለበት ይላሉ?

______________________________________________________________________________________________________________________________________________

በድጋሜ እናመሰግናለን፡፡

Page 92: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

1

አባሪ 7

በአማራ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጅ ተጽዕኖ

የምልከታ ቼክ ሊስት

የተጠኝው ተቋም ስም-

ተቋሙ የሚገኝበት ቦታ- ዞን ወረዳ

የሰራተኛ ብዛት- ወንድ- ሴት- ድምር-

Contact person- ስም

ስልክ

ኢ ሜይል

የተሰራጨ መጠይቅ መጠን

ተሞልቶ የተሰበሰበ መጠይቅ መጠን

1) የኢኮቴ መሳሪያዎች አቅርቦት

ተ.ቁ የዕቃው ዓይነት የሚሰራ የማይሰራ

1 ኮምፒውተር

2 ፕሪንተር

3 ስካነር

4 ፎቶኮፒ ማሽን

5 ፕላዝማ ቴሌቪዥን

6 ሰርቨር

7

Page 93: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

2

2) ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች

3) የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ ቤዞች አይነት

4) የ LAN ዝርጋታ ዓይነት

5) የለማው ድረ ገጽ አይነት

6) ወረዳ ኔቱ የሚሰጠው አገልግሎት

7) ሰኩል ኔቱ የሚሰጠው አገልግሎት

ተ.ቁ የመሰረተ ልማቱ አይነት አለው የለውም

1 የኢንተርኔት አገልግሎት

2 ወረዳ ኔት

3 ስኩል ኔት

4 ላን /LAN/ ዝርጋታ

5 የለሙ ሶፍትዌሮችና ዳታ

ቤዞች

6 የለማ ድረ ገጽ

7 የስልጠና ማዕከል

Page 94: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations
Page 95: The impact of ICT on public service in Amhara Region Governmental Organizations

4

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ካርታ